በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በተቃውሞ የሰነበቱት የዐማራ ክልል ከተሞች ወደ አንጻራዊ መረጋጋት እየተመለሱ


በተቃውሞ የሰነበቱት የዐማራ ክልል ከተሞች ወደ አንጻራዊ መረጋጋት እየተመለሱ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:32 0:00

በተቃውሞ የሰነበቱት የዐማራ ክልል ከተሞች ወደ አንጻራዊ መረጋጋት እየተመለሱ

የሰው ሕይወት የጠፋባቸው እና የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ግጭቶች እና የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ሲካሔድባቸው የሰነበቱት ልዩ ልዩ የዐማራ ክልል ከተሞች፣ ወደ አንጻራዊ መረጋጋት በመመለስ ላይ እንደኾኑ፣ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል፡፡
ዋነኛ ከሚባሉ ከተሞች በአንዳንዶቹም፣ ተዘግተው የነበሩ የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች፣ የግል አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እና የንግድ ድርጅቶች፣ ቀስ በቀስ ወደ ሥራ በመመለስ ላይ እንደኾኑ ነዋሪዎቹ አመልክተዋል፡፡
ለዐማራ ኮርፖሬሽንማብራሪያ የሰጡት፣ የክልሉ የብልጽግና ጽ/ቤት ሓላፊ አቶ ግርማ የሺጥላ፣ መንግሥት፥ የልዩ ኃይል አባላትን “ወደ ጸጥታ ተቋማት መልሶ ለማደራጀት” ያሳለፈው ውሳኔ ተቃውሞ የገጠመው፣ “አስቀድሞ ሕዝብ እንዲወያይበት በአለመደረጉ” እንደኾነ አስረድተዋል፡፡በቀጣይ፣ ከሕዝብ ጋራ ለመወያየት ዕቅድ መያዙንም አስታውቀዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG