ብዙኀን መገናኛዎች በብዛት የሚያተኩሩት በመጥፎ ዜናዎች ላይ ነው፤ የሚል ወቀሳ አዘውትሮ ይሰማል፡፡ የችግሮችን ቋጠሮ በውል ለመፍታት፣ የጽልመቱን መውጫ በጭላንጭል ለማየት የሚያግዘው መፍትሔ ተኮር ጋዜጠኝነት በፈንታው፤ ጋዜጠኞች በችግሮች ላይ ብቻ ያተኮረ ‘መርዶ ነጋሪ’ ዘገባ ማፍሰስ ብቻ ሳይኾን፣ ለችግሮቹ መፍትሔ አፍላቂ ሊኾኑ የሚችሉ ርምጃዎችንም በማጣመር እንዲዘግቡ ይረዳል።
ከዐሥር ዓመታት በፊት የተመሠረተው “የመፍትሔ ተኮር ጋዜጠኝነት ድርጅት”፣ እስከ አሁን ሦስት ሺሕ ለሚኾኑ ጋዜጠኞች ሥልጠና መስጠቱን መሥራቾቹ ይናገራሉ፡፡
ዘገባው የዲኖ ጃሂድ ነው፤ ቆንጅት ታየ ወደ ዐማርኛ መልሳዋለች።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁን 06, 2023
በኢትዮጵያ ሕፃናት ከትጥቃዊ ግጭት ሊጠበቁ እንደሚገባ ተመድ አሳሰበ
-
ጁን 06, 2023
የሂዩማን ራይትስ ዋችን ክስ የኢትዮጵያ መንግሥት አስተባበለ