ብዙኀን መገናኛዎች በብዛት የሚያተኩሩት በመጥፎ ዜናዎች ላይ ነው፤ የሚል ወቀሳ አዘውትሮ ይሰማል፡፡ የችግሮችን ቋጠሮ በውል ለመፍታት፣ የጽልመቱን መውጫ በጭላንጭል ለማየት የሚያግዘው መፍትሔ ተኮር ጋዜጠኝነት በፈንታው፤ ጋዜጠኞች በችግሮች ላይ ብቻ ያተኮረ ‘መርዶ ነጋሪ’ ዘገባ ማፍሰስ ብቻ ሳይኾን፣ ለችግሮቹ መፍትሔ አፍላቂ ሊኾኑ የሚችሉ ርምጃዎችንም በማጣመር እንዲዘግቡ ይረዳል።
ከዐሥር ዓመታት በፊት የተመሠረተው “የመፍትሔ ተኮር ጋዜጠኝነት ድርጅት”፣ እስከ አሁን ሦስት ሺሕ ለሚኾኑ ጋዜጠኞች ሥልጠና መስጠቱን መሥራቾቹ ይናገራሉ፡፡
ዘገባው የዲኖ ጃሂድ ነው፤ ቆንጅት ታየ ወደ ዐማርኛ መልሳዋለች።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
በማላዊ ለአሳዳጊ አልባ ሕፃናት መጠጊያ የኾነው ማዕከል
-
ጁላይ 27, 2024
በጠፈር ምርምር ትምህርት መርሐ ግብር የተመረቁ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ