በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ይዞታ በአምነስቲ ዓመታዊ ሪፖርት ቅኝት


የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ይዞታ በአምነስቲ ዓመታዊ ሪፖርት ቅኝት
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:44 0:00

ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ የአገሮችን የመብት አያያዝ የሚፈትሽበትን ዓመታዊ ሪፖርት ትላንት ይፋ አደረገ።

አምነስቲ በዓመታዊ የሰብአዊ መብቶች ሪፖርቱ፣ የግፍ ግድያዎችንና ሕገ ወጥ እስሮችን ጨምሮ በዓመቱ ውስጥ በተለይ በኢትዮጵያ ተፈጸሙ ያላቸውን መልከ ብዙ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ዘርዝሯል፡፡

ሪፖርቱ በቅድሚያ፣ “የፌደራል መንግሥት ለትግራይ የሚላከውን ሰብአዊ ርዳታ ማገዱን በመቀጠል፣ ከነሐሴ እስከ ኅዳር ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ደግሞ አቅርቦቶች ሙሉ በሙሉ እንዲቋረጡ አደረገ፤” ሲል ይንደረደራል፡፡ “በብዙ ሺሕዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች፣ የሕግ ጠበቃ ሳያገኙ እና ያለፍርድ መደበኛ ባልኾኑ የማቆያ ሥፍራዎች በዘፈቀደ ታስረው እንዲቆዩ ተደርገዋል፤” በማለትም ይቀጥላል።

“የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤት የሰጠው ትእዛዝ ተጥሶ እስር ላይ እንዲቆዩ ተደርገዋል፤” ያለው ሪፖርት አክሎም፣ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እና የታጠቁ ቡድኖች፣ በሰላማዊ ሰዎች ላይ የግፍ ግድያ መፈጸማቸውን፣ ይህም በአንዳንድ ኹኔታዎች ከጦር ወንጀል ሊቆጠር እንደሚችል ጠቁሟል።

XS
SM
MD
LG