በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሴቶች ከአመራርና ጠንካራ ዘገባዎች የተገለሉበት ጋዜጠኝነት


ሴቶች ከአመራርና ጠንካራ ዘገባዎች የተገለሉበት ጋዜጠኝነት
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:01 0:00

የዛሬው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን (ማርች 8) 'ፍትሃዊነት' በሚል መሪ ቃል ስለ ዕኩልነት ብቻ ማውራት በቂ አይበቃም” በሚል በዓለም ዙሪያ እየታሰበ ነው። ሴቶችን በፍትሃዊነት ካለምንም አድልዎ ማብቃትና ወደፊት ማምጣት አስፈላጊ መሆኑንም ያሳስባል።

በኢትዮጵያ ሴቶች ዕኩል ተወዳዳሪ ካልሆኑባቸው ዘርፎች መካከል የብሮድካስት መገናኛ ብዙሃን አንዱ መሆኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጋዜጠኝነት እና የተግባቦት ት/ቤት መምህር በሆኑት በዶክተር ሙላቱ አለማየሁ እና በመብቶች እና የዴሞክራሲ ዕድገት ማዕከል /ካርድ/ በቅርቡ የተሠራ አንድ ጥናት አመላክቷል። እስካሁን በሬዲዮ እና በቴሌቪዥን ዘርፉ የሚሠሩ ሴት ጋዜጠኞች ቁጥር ከጠቅላላው 25 ከመቶ ብቻ መሆኑን እና እነዚህ ሴቶች የዓመታት ልምድ ያካበቱም ቢሆኑ ወደ አመራር ደረጃ ከፍ አለማለታቸውን ጥናቱ ይጠቁማል።

ጥናቱን ያካሄዱት ዶ/ር ሙላቱ አለማየሁ እና ሁለት ሴት ጋዜጠኞች ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ቆይታ አድርገዋል። ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG