በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በዋስ እንዲለቀቁ የተወሰነላቸው ወንጌላዊ ቢኒያም ከእስር አልተፈቱም


በዋስ እንዲለቀቁ የተወሰነላቸው ወንጌላዊ ቢኒያም ከእስር አልተፈቱም
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:36 0:00

ሰሞኑን ከኢትዮጵያ ኦርቶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከነበረው ችግር ጋራ በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉት ግለሰቦች መካከል አንዱ የሆኑት ፓስተር ቢኒያም ሽታዬ ጉዳይ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት መሄዱን ጠበቃቸው ገለጹ።

ጥር 14/2015 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ተፈጥሮ ከነበረው ችግር ጋራ በተያያዘ በቁጥጥር ስር ከዋሉ ግለሰቦች መካከል የካቲት 3/2015 ዓ.ም የተያዙት ወንጌላዊ ቢኒያም ሽታዬ፣ ፖሊስ ሁከትና ብጥብጥ በመፍጠር ወንጀል ጠርጥሪያቸዋለሁ በሚል ፍርድ ቤት አቅርቧቸው ጉዳያቸውን በመከታተል ላይ እንደሚገኙ ከ33 ጠበቆቻቸው መካከል አንዱ ጠበቃና የህግ አማካሪ ብሩክ ደረጀ ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል፡፡

የካቲት 17 ቀን ፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት የ5,000 ብር ዋስትና አስይዘው እንዲወጡ ቢፈቀድም ፖሊስ ይግባኝ በማቅረብ በእስር ላይ እንዳቆያቸውም የገለጹት ጠበቃው፣ ጉዳያቸው አሁን ወደ አዲስ አበባ ፍርድ ቤት ወርዶ እየታየ መሆኑንም አብራርተዋል፡

በተለያዩ የፌዴራል ፍርድ ቤቶች ዋስትና ቢፈቀድላቸውም፣ ፖሊስ በፌዴራል ደረጃ ባሉ ፍርድ ቤቶች ያለውን ይግባኝ ካጠናቀቀ በኋላ፣ ዛሬ ጉዳዩን ወደ አዲስ አበባ ከተማ ፍርድ ቤት ንፋስ ስልክ ምድብ ችሎት ወስዶት እዚያም ዋስትና ተፈቅዶላቸው ፖሊስ ይግባኝ ማቅረቡን ከጠበቆቻቸው አንዱ ጠበቃ ብሩክ ደረጀ ተናግረዋል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ፡፡

XS
SM
MD
LG