በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ወልቂጤ አድማ ላይ ናት


ወልቂጤ አድማ ላይ ናት
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:35 0:00

በደቡብ ክልል ጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ ባለፈው ሳምንት በመጠጥ ውሃ ችግር ምክኒያት ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የወጡ ሦስት ሰዎች መገደላቸውን ተከትሎ የተደረገው ከቤት ውስጥ ያለመውጣት አድማ ዛሬም ቀጥሏል። ባንክ ቤቶችን ጨምሮ የመንግሥት እና የግል ተቋማት ዝግ መሆናቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል።

አድማውን ያደረጉት ሰላማዊ ሰዎችን ገድለዋል የተባሉ የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ለሕግ እንዲቀርቡና ለሟች ቤተሰቦች ካሳ እንዲከፈል ለማድረግ መሆኑን ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

ከተማው ወደ መደበኛ እንቅስቃሴ እንዲገባ ጥረት እያደረገ መሆኑን የገለፀው የደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አመፅ አስነስተዋል የተባሉ 15 ሰዎችን ማሰሩን ገልጿል።

ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ።

XS
SM
MD
LG