በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ኬንያ ሽፍቶችን የማጥፋት ዘመቻ ጀመረች


ኬንያ ሽፍቶችን የማጥፋት ዘመቻ ጀመረች
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:32 0:00

የኬንያ ደህንነት ኃይሎች ከሰሜን ስምጥ ሸለቆ አካባቢ ሽፍቶችን የማጽዳት ዘመቻ የጀመሩ ሲሆን ህገ ወጥ የጦር መሣሪያዎችንም ይዘዋል፡፡ ተችዎች በፖሊስ ተደግፎ የሚመራው የሠራዊቱ ዘመቻ ላልተገባ የሰብአዊ ጥቃት ሊያጋልጥ ይችላል ይላሉ፡፡

በሠራዊቱ የሚደገፈው የኬንያ ፖሊስ፣ በስምጥ ሸለቆ አካባቢ ማኅበረሰቡንና የጸጥታ ኃይሎችን የሚያጠቁትንና የሰዎችን ከብቶች የሚሰርቁትን ሽፍቶች ለመደመሰስ ዘመቻዎችን እያካሄደ ነው፡፡

የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ በኬኑክ ግዛት ቱርካና ወረዳ ውስጥ በተካሄዳባቸው የደፈጣ ጥቃት ሶስት ፖሊሶች ከተገደሉና ሌሎች ስምንት ሰዎች ከቆሰሉ በኋላ የዘመቻውን ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡፡

ሽፍቶቹ በሰሜን የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ ማኅበረሰቦችን ለአስርት ዓመታት ሲያጠቁ የቆዩና ከብቶችንም የዘረፉ ሲሆን ለብዙዎቹ ግጭቶችም ተጠያቂዎች ሆነዋል፡፡

የኬንያ ፖሊስ ኃላፊ ጃፌት ኩሜ ባላፈው ማክሰኞ የቱርካና ወረዳን ከጎበኙ በኋላ የማኅበረሰቡ አባላት እርስ በርሳቸው መጠቃቃትን እንዲያቆሙ አሳስበዋል፡፡

XS
SM
MD
LG