በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዳባት የተጠለሉ ተፈናቃዮች የገጠማቸው ፈተና


ዳባት የተጠለሉ ተፈናቃዮች የገጠማቸው ፈተና
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:53 0:00

ከሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ጋር በተያያዘ ከትግራይ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ “ሽመላኮ” በተባለው መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ተፈናቃዮች ከፍተኛ የምግብ እጥረት እንዳጋጠማቸው ተናግረዋል ።

ተፈናቃዮቹ እንደሚሉት ከጥቅምት መጨረሻ ወዲህ ምንም አይነት የምግብና ንፅህና መጠበቂያ ባለማግኘታቸው ህፃናት ልጆቻቸው ለበሽታ እየተጋለጡ ነው።

የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት በበኩሉ ችግሩ መኖሩን አምኖ በመጠለያ ጣቢያ ከሚገኙት በተጨማሪ ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው የሚኖሩ 41ሺ የሚሆኑ ተፈናቃዮች እርዳታ እያገኙ እንዳልሆነ አመልክቷል ።

የአማራ ክልል አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን በበኩሉ ከፌዴራል አደጋ ሥጋት አና ሥራ አመራር ኮሚሽን ጋር እየተነጋገርኩ ነው ብሏል።

XS
SM
MD
LG