ፊልም ለማህበረሰባዊ ንቃት ፡-ቆይታ ከጋዜጠኛ እና ፊልም ባለሙያ ማንተጋፍቶት ስለሺ ጋር
መኖሪያውን በጀርመን ሀገር ያደረገው ማንተጋፍቶት ስለሺ በብዙዎች ዘንድ ከሚታወቅበት የጋዜጠኝነት ስራው ባሻገር ዓለም አቀፋዊ ሽልማቶችን ያሸነፈ የፊልም ባለሙያ ነው ። ከዚህ በፊት "ግርታ " የተሰኘው ፊልሙ የወጣት አፍሪካዊያን የፊልም ፌስቲቫል እና ዛንዚባር ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በአራት ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር ትልቅ ክብር የሚሰጠው ፣ "የአፍሪካ ኦስካር " ተብሎ በሚጠራው የፓን አፍሪካ የፊልም እና ቴሌቭዥን ፌስቲቫል ላይም ዕጩ ሆኗል።በተለይ ማህበረሰባዊ አንድምታ ባላቸው አጫጭር ፊልሞች ላይ ትኩረቱን ያደረገው ማንተጋፍቶት ፣በቅርቡ "የበረንዳው ንጉስ" የተሰኘ አጭር ፊልም ለተመልካች አቅርቧል ። ይህ ፊልም የካሊፎርኒያ ሲሊከን ቫሊ የአፍሪካ ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በተለያዩ ከፊልም ጋር ተያያዥ በሆኑ መድረኮች ላይ እየታየ ይገኛል። አዲሱን ፊልሙን መነሻ አድርገን ከማንተጋፍቶት ጋር ተያያዥ ሀሳቦችን መዘናል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ኦክቶበር 03, 2023
ዋይት ሐውስ ለዩክሬን ድጋፉ እንዲቀጥል ጥረት እያደረገ ነው
-
ኦክቶበር 03, 2023
በኬንያ መንግሥት የሃይቲ የፖሊስ ስምሪት ውሳኔ ላይ ዜጎች ጥያቄ እያነሡ ነው
-
ኦክቶበር 03, 2023
ክልሎች የትምህርት ዘመኑን የተማሪዎች ምዝገባ ዕቅዳቸውን እንዳላሳኩ እየገለጹ ነው
-
ኦክቶበር 03, 2023
በፈተናዎች ንብርብር ውስጥ ለሚገኘው የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሻሻሉ ተስፋዎች አሉ?
-
ኦክቶበር 03, 2023
በሶማሌ ክልል የቆሎጂ መጠለያ ጣቢያ ስድስት ሰዎች እንደተገደሉ ኢሰመኮ ገለጸ
-
ኦክቶበር 03, 2023
የሲዳማ ፌዴራሊስት ፓርቲ ሦስት አባላቱ ያለሕግ እንደታሰሩበት ገልጿል