ፊልም ለማህበረሰባዊ ንቃት ፡-ቆይታ ከጋዜጠኛ እና ፊልም ባለሙያ ማንተጋፍቶት ስለሺ ጋር
መኖሪያውን በጀርመን ሀገር ያደረገው ማንተጋፍቶት ስለሺ በብዙዎች ዘንድ ከሚታወቅበት የጋዜጠኝነት ስራው ባሻገር ዓለም አቀፋዊ ሽልማቶችን ያሸነፈ የፊልም ባለሙያ ነው ። ከዚህ በፊት "ግርታ " የተሰኘው ፊልሙ የወጣት አፍሪካዊያን የፊልም ፌስቲቫል እና ዛንዚባር ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በአራት ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር ትልቅ ክብር የሚሰጠው ፣ "የአፍሪካ ኦስካር " ተብሎ በሚጠራው የፓን አፍሪካ የፊልም እና ቴሌቭዥን ፌስቲቫል ላይም ዕጩ ሆኗል።በተለይ ማህበረሰባዊ አንድምታ ባላቸው አጫጭር ፊልሞች ላይ ትኩረቱን ያደረገው ማንተጋፍቶት ፣በቅርቡ "የበረንዳው ንጉስ" የተሰኘ አጭር ፊልም ለተመልካች አቅርቧል ። ይህ ፊልም የካሊፎርኒያ ሲሊከን ቫሊ የአፍሪካ ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በተለያዩ ከፊልም ጋር ተያያዥ በሆኑ መድረኮች ላይ እየታየ ይገኛል። አዲሱን ፊልሙን መነሻ አድርገን ከማንተጋፍቶት ጋር ተያያዥ ሀሳቦችን መዘናል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 14, 2025
በአፍሪካ የኅይል አቅርቦት ላይ ያተኮረውና በዋሽንግተን ዲሲ የተካሔደው ጉባኤ
-
ማርች 14, 2025
የኢትዮጵያውያት ሴቶች ጥያቄ ምንድን ነው? - የአድማጭ ተመልካቾች አስተያየት
-
ማርች 13, 2025
አርቲስት አንዱዓለም ጎሣ ተጨማሪ 13 ቀናትን በእስር እንዲቆይ ፍርድ ቤት ፈቀደ
-
ማርች 13, 2025
ሩሲያ የተቆጣጠረቻቸውን የዩክሬን ግዛቶች እንደያዘች መቀጠል ትሻለች