ፊልም ለማህበረሰባዊ ንቃት ፡-ቆይታ ከጋዜጠኛ እና ፊልም ባለሙያ ማንተጋፍቶት ስለሺ ጋር
መኖሪያውን በጀርመን ሀገር ያደረገው ማንተጋፍቶት ስለሺ በብዙዎች ዘንድ ከሚታወቅበት የጋዜጠኝነት ስራው ባሻገር ዓለም አቀፋዊ ሽልማቶችን ያሸነፈ የፊልም ባለሙያ ነው ። ከዚህ በፊት "ግርታ " የተሰኘው ፊልሙ የወጣት አፍሪካዊያን የፊልም ፌስቲቫል እና ዛንዚባር ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በአራት ዓለም አቀፍ የፊልም ፌስቲቫሎች ላይ አሸናፊ ከመሆኑ ባሻገር ትልቅ ክብር የሚሰጠው ፣ "የአፍሪካ ኦስካር " ተብሎ በሚጠራው የፓን አፍሪካ የፊልም እና ቴሌቭዥን ፌስቲቫል ላይም ዕጩ ሆኗል።በተለይ ማህበረሰባዊ አንድምታ ባላቸው አጫጭር ፊልሞች ላይ ትኩረቱን ያደረገው ማንተጋፍቶት ፣በቅርቡ "የበረንዳው ንጉስ" የተሰኘ አጭር ፊልም ለተመልካች አቅርቧል ። ይህ ፊልም የካሊፎርኒያ ሲሊከን ቫሊ የአፍሪካ ፊልም ፌስቲቫልን ጨምሮ በተለያዩ ከፊልም ጋር ተያያዥ በሆኑ መድረኮች ላይ እየታየ ይገኛል። አዲሱን ፊልሙን መነሻ አድርገን ከማንተጋፍቶት ጋር ተያያዥ ሀሳቦችን መዘናል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 05, 2023
በድባቴ እና እራስን በማጥፋት ስሜት ውስጥ ያሉ ወጣቶች ስለአዕምሮ ጤና የሚወያዩበት ቡድን
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
ጠያቂ ፊልሞች - ቆይታ ከፊልም ባለሞያ አቤል መካሻ ጋር
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
ለመጀመሪያ ጊዜ በአኝዋክ ቋንቋ የተፃፉት የህፃናት መፅሃፍት
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
በሜሪላንድ ግዛት የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሊጀመር ነው
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
በጦርነቱ 3.2 ቢሊዮን ብር የሚገመት የውሀ መሰረተልማት መውደሙ ተገለፀ
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
የተፈናቃዮች ቁጥር በአማራ ክልል መጨመሩን ተመድ አስታወቀ