No media source currently available
አዲስ አበባ ተወልዶ ያደገው ዳግም ገብሬ ፣ በተፈጥሮ የተሰጠውን የስዕል ጥበብ በማህበራዊ አውታሮች ላይ ካገኛቸው ማስተማሪያዎች ጋር አቀናጅቶ ቀልብ ሳቢ ስራዎችን ለዕይታ ያበቃ ወጣት ነው ።ዳግም በተለይ በክር በሚሰራቸው የዕደ ጥበብ ስራዎች መልካም ምላሽን ከማግኘቱ በተጨማሪ አትራፊ የመተዳደሪ መላም ሆኖታል። ዕወቀቱን ለሌሎች ወጣቶች በማካፈል ላይም ይገኛል። የአዲስ አበባው ዘጋቢያችን ገ/ሚካኤል ገ/መድህን ከዳግም ጋር አጭር ቆይታ አድርጓል ።