በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ዶ/ር ደብረጽዮን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን አመሰገኑ


ዶ/ር ደብረጽዮን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን አመሰገኑ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:27 0:00

ዶ/ር ደብረጽዮን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን አመሰገኑ

በኢትዮጵያ መንግሥትና በህወሃት መካከል የሰላም ስምምነት መፈረሙን ተከትሎ በኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈጉባኤ ታገሰ ጫፎ የተመራውና ሚኒስትሮችና የተለያዩ ተቋማት ኃላፊዎች የተካተቱበት ልዑካን ቡድን በመቀሌ ተገኝተው የተቋረጡ መሰረተ ልማቶችን በማስቀጠል ላይ ውይይት አድርገዋል።
ልዑካኑ ከትግራይ ክልል መሪ ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤልና በክልሉ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ከተወከሉ አካላት ጋራ ተገናኝተው ተወያይተዋል። ዶ/ር ደብረጽዮን የልዑካን ቡድኑን አባላት ያመሰገኑ ሲሆን፤ “ጠቅላይ ሚኒስትር አብይን በጣም ደግሞ በከፍተኛ ደረጃ ማመስገን እፈልጋለሁ” ብለዋል።

ዛሬ በመቀሌ የአንድ ቀን ቆይታ ባደረገው የኢትዮጵያ መንግሥት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ውስጥ ከተካቱት ባለሥልጣናት መካከል የአገልግሎት ሰጭ ተቋማት የበላይ ኃላፊዎችም ይገኙበታል። ባለሥልጣናቱ የአንድ ቀን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አዲስ አበባ ማምሻውን ተመልሰዋል።
እነዚሁ የኢትዮ-ቴሌኮም፣የመብራት ሃይል፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የመንገዶች ባለስልጣን እና የሌሎችም ተቋማት የበላይ ሃላፊዎች አገልግሎት እየተጀመረ ባለበት ሂደትና በተያያዥ ጉዳዮች ላይ ከመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ተወያይተዋል።

/ዝርዝሩ ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

XS
SM
MD
LG