በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ነው


ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ነው
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:13 0:00

ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ ነው

የኢትዮጵያ መንግሥትና ህወሓት ያደረጉትን የሠላም ሥምምነት ተከትሎ ተጨማሪ እርዳታ ወደ ትግራይ ክልል እየገባ መሆኑን ለጋሽ ድርጅቶች እየገለጹ ነው።

ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ እና የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር (ዩኤንኤችሲአር)፣ የተለያዩ የሕይወት አድን ሰብዓዊ እርዳታ የጫኑ ተሸከርካሪዎች ዛሬ ትግራይ ክልል መድረሳቸውን ገልጸዋል፡፡

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ደግሞ ቅዳሜ ዕለት መቀሌ እና ሽሬ ከተሞች የእርዳታ ምግብና ነዳጅ ማድረሱን ገልጾ፣ ተደራሽነቱን በየቀኑ ለማድረግ መዘጋጀቱን ይፋ አድርጓል፡፡ በአየር በረራም ዕርዳታ እያደረሱ መሆኑን ለጋሽ ድርጅቶቹ ገልጸዋል፡፡

/ሙሉውን ከተያያዘው ፋይል ይከታተሉ/

XS
SM
MD
LG