በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ


የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ
please wait

No media source currently available

0:00 0:10:13 0:00

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማብራሪያ

በፌዴራል መንግስትና በህወሃት መካከል የሰላም ስምምነት ከተፈረመ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ከአባላት ለተነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስምምነቱ ተግባራዊነት መንግሥታቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል።

“በአሸባሪነት ከተፈረጀ አካል ጋር እንዴት ድርድር ተፈጸመ?” በሚል ለተነሳላቸው ጥያቄ የኢትዮጵያ ሕግ ይህን እንደማይከለክል ገልጸው ዓለም አቀፍ ልምዶችን በመጥቀስ ምላሽ ሰጥተዋል።

የትግራይና የአማራ ክልሎች በይገባኛል የሚወዛገቡበትን ስፍራ በተመለከተ በሰጡት ምላሽ “የፕሪቶሪያው ድርድር ይህን የሚመለከት አይደለም” በሚል መልሰዋል፡፡ ጉዳዩ ዘላቂ መፍትሔ በሚያመጣ መልኩ ሕጋዊ እልባት እንደሚሰጠውም አብራርተዋል፡፡

የሰላም ስምምነቱን በተመለከተ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማብራሪያ እስካሁን ከህወሃት በኩል በቀጥታ የተሰጠ ምላሽና አስተያየት የለም፡፡

XS
SM
MD
LG