በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ባይደን ማሪዋና እጽ በመያዝ ለተወነጀሉት በሙሉ ምህረት አደረጉ


ባይደን ማሪዋና እጽ በመያዝ ለተወነጀሉት በሙሉ ምህረት አደረጉ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:02 0:00

ባይደን ማሪዋና እጽ በመያዝ ለተወነጀሉት በሙሉ ምህረት አደረጉ

ፕሬዚዳንት ባይደን አነስተኛ መጠን ያለውን ማሪዋና ሱስ አስያዥ እጽ ይዘው በመገኘት በፌዴራል መንግሥት ተከሰው ለተፈረደባቸው 6ሺ 500 ሰዎች ምህረት አድርገዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ባይደን ትናንት ሀሙስ የሰጡትን ምህረት ይፋ ባደረጉበት ወቅት "የማሪዋና ጉዳይ በአግባቡ ባለመያዙ የብዙ ሰዎች ህይወት ተሰናክሏል" ብለዋል።

አነስተኛ መጠን ያለው የማሪዋና እጽ ይዘው በመገኘት የፌዴራሉን ህግ ተላልፈዋል በሚል ለተከሰሱት ሰዎች ምህረት ያደረጉት ባይደን፣ የየክፍለ ግዛቶቹ አገረ ገዥዎችም ተመሳሳዩን እንዲያደርጉ አሳስበዋል፡፡

[ሙሉውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ]

XS
SM
MD
LG