በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

አንገላ መርከል የናንሰን ሽልማት አሸናፊ ሆኑ


አንገላ መርከል የናንሰን ሽልማት አሸናፊ ሆኑ
please wait

No media source currently available

0:00 0:02:59 0:00

የቀድሞ የጀርመን ቻንስለር አንገላ መርከል ከሦሪያ ጥቃትና ግድያን ሸሽተው ለወጡ ከ1.2 ሚሊዮን በላይ ስደተኞችና ጥገኝነት ጠያቂዎች መጠጊያ በመፍጠራቸው ከፍተኛው የተባበሩት መንግሥታት የስደተኞች ኮሚሽን ሽልማት የሆነውን፣ የናንሰንን ሽልማት አሸንፈዋል፡፡

አንገላ መርከል የሦሪያው ጦርነት ከፍተኛ ደረጃ በደረሰበት እአአ በ2015 እና 2016 በነበረው ጊዜ ሌሎች አገሮች ፊታቸውን ያዞሩባቸውን የሦሪያ ስደተኞች በደስታ ተቀብለዋል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት የሥደተኞች ኮሚሽን (ዩኤንኤችሲአር) ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ መርከል ከአንድ ሚሊዮን የሚበልጡ ስደተኞች ህይወት በማትረፍና መልሰው እንዲቋቋሙ ለመርዳት የፖለቲካ ቁርጠኝነት እና ትልቅ የሞራል ልዕልና አሳይተዋል ሲሉ በሽልማቱ ሥነ ሥርዓት ወቅት ተናግረዋል፡፡

መርከል የስደተኞችን ችግር ዓለም አቀፍ ትኩረት እንዲያገኝ ረድተዋል ያሉት የዩኤንኤችሲአር ቃል አቀባይ ማቲው ሶልት ማርሽ ፈታኝ የሆኑ ሁኔታዎች ሲገጥሙ ፖለቲከኞች ኃላፊነትን ወደሌሎች ከማሸጋገር ይልቅ መፍትሄ ሊያመጣ የሚችል ሥራ ሲሰሩ ምን ውጤት ሊያመጡ እንደሚችሉ መርከል አሳይተዋል ብለዋል፡፡

XS
SM
MD
LG