በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በሶማሊያ ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲነሳ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጠየቁ


በሶማሊያ ላይ የተጣለው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲነሳ ኢትዮጵያ እና ሶማሊያ ጠየቁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:29 0:00

ላለፉት 30 ዓመታት በሶማሊያ ላይ ተጥሎ የቆየው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ እንዲነሳ ኢትዮጵያ ከሶማሊያ ጋር በመሆን ጥሪ አቀረበች

የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼህ ሞሀሙድ በኢትዮጵያ ባደረጉትን የሁለት ቀናት ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ማጠቃለያ ላይ የሁለቱ ሀገራት መሪዎች በሰጡት የጋራ መግለጫ፣ የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ማዕቀቡ እንዲነሳ በሶማሊያ መንግሥት የቀረበውን ጥሪ እንዲቀበል ጥሪ ማቅረባቸው ተገልጿል፡፡

ለቀጣናው ሰላምና መረጋጋት የሚያደርጉትን ጋራ ጥረጥ ሊያደናቅፉ የሚችሉ ያሏቸውን ያልተገቡ የውጭ ጣልቃ ገብ ተጽዕኖዎችን መቀነስ እንደሚገባና ሽብርተኝነትን በተሳካ ሁኔታ መዋጋት እንደሚገባ አፅንዖት መስጠታቸውንም የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት አስታውቋል፡፡

የሶማሊያው ፕሬዚዳንት የኢትዮጵያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ዛሬ ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡

XS
SM
MD
LG