በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የውጭ የገንዘብ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ


የውጭ የገንዘብ ድርጅቶች በኢትዮጵያ ገበያ ውስጥ
please wait

No media source currently available

0:00 0:07:57 0:00

የውጭ የገንዘብ ኩባንያዎችን ለማስገባት የፋይናንስ አዋጅ ማሻሻያ እየተደረገ መሆኑን ብሔራዊ ባንክ አስታውቋል።

ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎት ሥርዓት በኅብረተሰቡ ዘንድ የፋይናንስ ተደራሽነትን እንደሚያሰፋ የኢኮኖሚ ባለሙያዎች ይናገራሉ።

በቅርቡ ኢትዮ-ቴሌኮም ከዳሽን ባንክ ጋር በመተባበር ያስጀመረው የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎትም አነስተኛ ብድር ለሚፈልጉ የንግድ ተቋማት ትልቅ ዕድል ይዞ እንደመጣ ይገልፃሉ።

ይህ ሥርዓት በተለመደው የባንክ አሠራር ተጠቃሚ ያልሆኑትን የንግድ ሥራዎችና የኅብረተሰብ ክፍሎችን ለማካተት እንደሚያስችል ባለሙያዎቹ ጠቁመዋል።

ዘርፉ ጥብቅ ቁጥጥር ካልተደረገበት ችግር ሊያስከትል እንደሚችል የተነገረ ሲሆን በተጠቃሚው ዘንድም በአገልግሎቱ ላይ ዕውቀት ማስጨበጥ እንደሚያስፈልግ ቪኦኤ ያነጋገራቸው የኢኮኖሚ ባለሙያ ገልፀዋል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ።

XS
SM
MD
LG