እ.አ.አ በ2022 መገባደጃ ህዳር ወር ላይ ለሚካሄደው የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት እና አካባቢ ምርጫ ከሚወዳደሩ ተፎካካሪዎች መካከል በቨርጂንያ ክፍለ ግዛት የሚገኙትን አርሊንግተን፣ አሌክዛንድሪያ አና ደቡባዊውን የፌርፋክስ አካባቢ ወክሎ የሚወዳደረው ትውልደ ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊው ቴዲ ፍቅሬ አንዱ ነው። እንደ ቦዝ አለን የመሳሰሉ ትላልቅ ኩባንያዎች በቴክኖሎጂ ባለሙያነት ያገለገለው ቴዲ ከሰባት አመት በፊት ስራውን በማጣቱ ለሁለት አመት ተኩል በጎዳና ላይ ለመኖር ተገዶ የነበረ ሲሆን ያ ወቅት በሰዎች ላይ የሚደርሰውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነት እንዲመለከት እና ለምክር ቤት ምርጫ እንዲወዳደር እንደገፋፋው ገልጿል።
የጎዳና ህይወትን አልፎ ለአሜሪካ ምክርቤት ምርጫ የሚወዳደረው ትውልደ ኢትዮጵያዊ
እ.አ.አ በ2022 መገባደጃ ለሚካሄደው የአሜሪካ ምክርቤት ምርጫ ከሚወዳደሩ መካከል በቨርጂንያ ክፍለ ግዛት በአርሊንግተን፣ አሌክዛንድሪያ አና ደቡብ ፌርፋክስ የሚወዳደረው ትውልደ ኢትዮጵያዊ አሜሪካዊው ቴዲ ፍቅሬ አንዱ ነው። የቴክኖሎጂ ባለሙያው ቴዲ ከሰባት አመት በፊት ስራውን በማጣቱ ለሁለት አመት ተኩል በጎዳና ላይ የኖረ ሲሆን ያ ጊዜ በሰዎች ላይ የሚደርሰውን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ኢፍትሃዊነት እንዲመለከት እና ለምክር ቤት ምርጫ እንዲወዳደር እንደገፋፋው ገልጿል።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
በማላዊ ለአሳዳጊ አልባ ሕፃናት መጠጊያ የኾነው ማዕከል
-
ጁላይ 27, 2024
በጠፈር ምርምር ትምህርት መርሐ ግብር የተመረቁ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ