በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ ገዳይ በሽታዎች በአፍሪካ


ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ ገዳይ በሽታዎች በአፍሪካ
please wait

No media source currently available

0:00 0:04:25 0:00

በአፍሪካ እየጨመረ የመጣውን እንደ ዝንጀሮ ፈንጣጣ እና ኢቦላ ያሉ ከእንስሳት ወደ ሰው የሚተላለፉ ገዳይ በሽታዎች መዛመት ለመግታት እርምጃ ይወሰድ ዘንድ የዓለም ጤና ድርጅት ጥሪ አቀረበ።

በአፍሪቃ ከእንስሳት ወደ ወደ ሰው የሚተላለፉ በሽታዎች መጠን ከቀደሙ አስርት ዓመታት ጋር ሲነጻጸር እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ2012 እስከ 2022 ዓ/ም ባለው ጊዜ ውስጥ በ63 በመቶ መጨመሩን የዓለም ጤና ድርጅት ይፋ ያደረገው አዲስ የጥናት ዘገባ አመለከተ።

እንደ ዘገባውም በዓለም ዙሪያ የሰውን ልጅ ከሚያጠቁት ተላላፊ በሽታዎች 60 ከመቶው እና አዲስ ከሚከሰቱት ደግሞ ከ75 በመቶው በላይ የሚሆኑት የዱር እና የቤት እንስሳትን በሚያጠቁ በሽታ አምጪ ተህዋሲያን የሚከሰቱ ናቸው።

በእነኚህ በሽታዎች ሳቢያም በዓለም ዙሪያ በየዓመቱ ቁጥሩ አንድ ቢሊዮን የሚጠጋ ሰው ለሕመም ሲጋለጥ ሚልዮኖች ደግሞ ለህልፈት ይዳርጋሉ።

XS
SM
MD
LG