በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሀገሪቱ መሪ ስልጣን እስኪለቁ ድረስ ፣ ከቤተመንግስት እንደማይወጡ የሲሪ ላንካ ተቃውሞ ሰልፈኞች አስታወቁ


.
.

የሀገራቸውን ፕሬዚደንት ጎታባያና ራጃፓክሳ መኖሪያ ቤት በመቆጣጠር ፣ በሀገሪቱ የባህር ኃይል ድጋፍ እንዲሸሹ ብሎም ከስልጣን እንዲለቁ ያደረጉት የሲሪ ላንካ ተቃዋሚ ሰልፈⶉች አሁንም ከፕሬዚደንቱ መኖሪያ ቤት ለመልቀቅ አልፈቀዱም ።

የተማሪዎች እንቅስቃሴ ፕሬዚደንት የሆነው ፣ ላሂሩ ዊራስካራ “ትግላችን ገና አላበቃም!” ሲል ለዘጋቢዎች ተናግሯል፣ በአሁኑ ሰዓት በደሴቲቱ ደቡባዊ የባህር ወሰን ላይ በሚገኝ መርከብ ውስጥ የተጠለሉት ራጃፓክሳ ፣ ከስልጣን መልቀቃቸውን ረቡዕ ዕለት ካስታወቁ በኃላ፣ ከስልጣን የመልቀቃቸው ነገር እርግጥ እስኪሆን ድረስ ፣ ትግሉ እንደማይቆም ዊራስካራ አክሏል ።

የቅዳሜው ዕለት ክስተት ፣ በደቡባዊ እስያዊት ደሴት የደረሰው ያልተጠበቀ ኢኮኖሚያዊ ቀውስ እና የራጃፓክሳ ቡድን የአመራር ድክመት እና ሙስና የቀሰቀሰው ለወራት የዘለቀው የተቃውሞ እንቅስቃሴ ጣሪያ ተደርጎ ተቆጥሯል።

በመቶሺ የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ዜጎች ራጃፓክሳ ፣ በአንድ ወቅት በተነጻጻሪነት ሀብታም የነበረችውን ሀገር በማሽመድመድ በህዝቧ ላይ መከራን ላመጣው፣ የመድሃኒት ፣ ምግብ እና ነዳጅ እጥረት ኃላፊነት እንዲወስዱ ነበር ለተቃውሞ የወጡት።

በቅኝ ግዛት ዘመን የተገነባውን፣ የፕሬዚደንቱን ቤተመንግስት ሰብረው የገቡት ተቃዋሚዎች፣ በቅንጡ ክፍሎች ውስጥ ተሰይመዋል፣ በመዋኛ ገንዳው ውስጥ ተምነሽንሸዋል፣ የፕሬዚደንቱን አልባሳት ፈትሸዋል ።

ይሄ ከመሆኑ አስቀድሞ፣ ራጃፓክሳ እንዲያመልጡ ለመርዳት ወታደሮች ወደ ሰማይ የተኮሱ ሲሆን፣ ፕሬዚደንቱ የባህር ኃይል ጀልባ እንዲሳፈሩ ተደርገው ለደህንነታቸው ወደ ሀገሪቱ ደቡባዊ ውሃማ ቀጠና ተወስደዋል ።

በዛሬው ዕለት ለሁሉም ዜጋ ክፍት በነበረው የፕሬዚደንቱ መኖሪያ ውስጥ ህጻናት እና ወላጆቻቸው በስፍራው የሚገኘውን ፒያኑ ሲቆረቁሩ፣ ቅንጡ የጥበብ ስራዎችን ሲያደንቁ፣ በፕሬዚደንቱ ወንበር ላይ በየተራ ሲቀመጡ ውለዋል። ዘገባው የኤ ኤፍፒ ነው።

XS
SM
MD
LG