በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ፅንስን በማቋረጥ ጉዳይ አዲሱ የአሜሪካ አቅጣጫና አንድምታ በኢትዮጵያዊያን ሴቶች ላይ ያለው


ፅንስን በማቋረጥ ጉዳይ አዲሱ የአሜሪካ አቅጣጫና አንድምታ በኢትዮጵያዊያን ሴቶች ላይ ያለው
please wait

No media source currently available

0:00 0:09:01 0:00

ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ “በሮ እና በዌድ መካከል ያለ ሙግት ጉዳይ” ተብሎ የሚጠራውና ላለፉት ሃምሣ ዓመታት ሲሠራ የቆየውን ፅንስን ለማቋረጥ ፌደራል ህገመንግሥታዊ ከለላ ሲሰጥ የቆየውን ህግ ጠቅላይ ፍርድ ቤቷ በቅርቡ ገልብጦታል።

ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ጉዳዮች ወደ ስቴቶቹ መልሶ ፅንስን በማቋረጥ ጉዳይ በራሳቸውን እንዲወስኑ ፈቅዷል።

ይህ ሁኔታ አሜሪካ ውስጥ ከፍተኛ ውዝግብ ያስነሳና የፖለቲካ ጉዳይ ከመሆኑ በተጨማሪ በዓለምአቀፍ ደረጃም በወሊድ መከላከያና ፅንስን በማቋረጥ አገልግሎቶች ላይም የሰፉ ተግዳሮቶችን መደቀኑን ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው።

ለመሆኑ ይህ አዲስ አቅጣጫ በአፍሪካዊያን በአጠቃላይ፣ በተለይ ደግሞ በኢትዮጵያዊያን ሴቶችና በጤናቸው ላይ የሚያሳድረው ጫና ይኖር ይሆን?

የማሪ ስቶፕስ ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ዳይሬክተርን፣ በጋንዲ መታሰቢያ ሆስፒታል የአንድ መስኮት አገልግሎት ሰጭ ሃኪምና ሴቶችን አነጋግረናል።

ዝርዝሩን ከተያያዘው ፋይል ያገኛሉ

XS
SM
MD
LG