“አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው”ደራሲ እና ሀያሲ ዳንኤል ወርቁ
ቁጥራቸው በበዛ የራዲዮ እና የቴሌቭዥን ድራማዎች ደራሲነቱ እና አዘጋጅነቱ የሚታወቀው ሰለሞን ዓለሙ በተወለደ በ62 ዓመቱ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ተለይቷል። በመቶዎች የሚቆጠሩ የጥበብ ሥራዎችን ለአድማጭ እና ለተመልካች ያቀረበው አንጋፋው የኪነጥበብ ሰው ነገ ረቡዕ ሰኔ 22 /2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ከሰዓት በኃላ አድናቂዎቹ በሚገኙበት የክብር ሽኝት እንደሚደረግለት፤ የቀብር ሥነ ስርዓቱም ሰዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም ታውቋል። ከቅርብ ጓደኞቹ አንዱ የሆነው ደራሲ፣ተርጓሚን ሐያሲ ዳንኤል ወርቁ “አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው” ብሎናል። /ሀብታሙ ስዩም የዕውቁን ከያኒ የቅርብ ጓደኞች እና የስራ አጋሮች ጠይቆ ያሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
በማላዊ ለአሳዳጊ አልባ ሕፃናት መጠጊያ የኾነው ማዕከል
-
ጁላይ 27, 2024
በጠፈር ምርምር ትምህርት መርሐ ግብር የተመረቁ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች
-
ጁላይ 26, 2024
የኢትዮጵያውያኑ ባህላዊ ማዕድ እና አብሮነት ታዛ - በሚልዋኪ
-
ጁላይ 26, 2024
የፕሬዝደንት ጆ ባይደን ንግግር
-
ጁላይ 23, 2024
አምስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን በኮዲንግ ሞያ የማብቃት መርሐ ግብር ይፋ ኾነ