“አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው”ደራሲ እና ሀያሲ ዳንኤል ወርቁ
ቁጥራቸው በበዛ የራዲዮ እና የቴሌቭዥን ድራማዎች ደራሲነቱ እና አዘጋጅነቱ የሚታወቀው ሰለሞን ዓለሙ በተወለደ በ62 ዓመቱ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ተለይቷል። በመቶዎች የሚቆጠሩ የጥበብ ሥራዎችን ለአድማጭ እና ለተመልካች ያቀረበው አንጋፋው የኪነጥበብ ሰው ነገ ረቡዕ ሰኔ 22 /2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ከሰዓት በኃላ አድናቂዎቹ በሚገኙበት የክብር ሽኝት እንደሚደረግለት፤ የቀብር ሥነ ስርዓቱም ሰዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም ታውቋል። ከቅርብ ጓደኞቹ አንዱ የሆነው ደራሲ፣ተርጓሚን ሐያሲ ዳንኤል ወርቁ “አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው” ብሎናል። /ሀብታሙ ስዩም የዕውቁን ከያኒ የቅርብ ጓደኞች እና የስራ አጋሮች ጠይቆ ያሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ኦገስት 12, 2022
የዩክሬን ስደተኞች በእንግሊዝ የሠራተኛ እጥረትን እያቃለሉ ነው
-
ኦገስት 12, 2022
የታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ሦስተኛ ዙር የውሃ ሙሌት መጠናቀቁ ይፋ ሆነ
-
ኦገስት 12, 2022
አሜሪካ ከአፍሪካ ጋር “እውነተኛ አጋርነት” እንዲኖር ትፈልጋለች - ብሊንከን
-
ኦገስት 12, 2022
ውጥረት እየሸተተበት የመጣው የኬንያ ምርጫ