“አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው”ደራሲ እና ሀያሲ ዳንኤል ወርቁ
ቁጥራቸው በበዛ የራዲዮ እና የቴሌቭዥን ድራማዎች ደራሲነቱ እና አዘጋጅነቱ የሚታወቀው ሰለሞን ዓለሙ በተወለደ በ62 ዓመቱ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ተለይቷል። በመቶዎች የሚቆጠሩ የጥበብ ሥራዎችን ለአድማጭ እና ለተመልካች ያቀረበው አንጋፋው የኪነጥበብ ሰው ነገ ረቡዕ ሰኔ 22 /2014 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ከሰዓት በኃላ አድናቂዎቹ በሚገኙበት የክብር ሽኝት እንደሚደረግለት፤ የቀብር ሥነ ስርዓቱም ሰዓት በቅድስት ስላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀም ታውቋል። ከቅርብ ጓደኞቹ አንዱ የሆነው ደራሲ፣ተርጓሚን ሐያሲ ዳንኤል ወርቁ “አንድ ትልቅ የኪነጥበበ ፈጣሪ እንዳጣን ነው የማስበው” ብሎናል። /ሀብታሙ ስዩም የዕውቁን ከያኒ የቅርብ ጓደኞች እና የስራ አጋሮች ጠይቆ ያሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፋይል ያዳምጡ/
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 10, 2025
ቀይ መስቀል ማኅበር የሰብአዊነት ትምሕርት ቤት አቋቋመ
-
ፌብሩወሪ 10, 2025
“ደራሮ” የምስጋና በዓል በጌዴኦ
-
ፌብሩወሪ 09, 2025
አይ.ኤም ኤፍ እስከ አኹን ወደ1.5 ቢሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ መልቀቁን ኃላፊዋ ገለጹ
-
ፌብሩወሪ 08, 2025
የፖለቲካ ምርጫ እና ጭንቀት
-
ፌብሩወሪ 06, 2025
ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ