ኢትዮጵያ የስደተኞችን ደህንነት ለማስጠበቅ ምን እየሰራች ነው?
በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ ከ800 ሺ በላይ ስደተኞችን በግዛቷ በማስጠለል ፣ በብዛት ስደተኞችን ከአስተናገዱ የአፍሪካ ሀገራት ሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሀገር ናት። ሀገሪቱ በቅርብ ጊዜያት በርስበርስ ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል። ።የጦርነቱ ጉዳት በዜጎቿ ላይ ብቻ ሳይሆን የተሻለ ህይወት ፈልገው በግዛቷ ለተጠለሉት ስደተኞችም መትረፉን የተለያዩ ሪፖርቶች ያሳያሉ ። የመጠለያ ጣቢያዎች ውድመት፣ የጭካኔ ተግባራት እና ሞት በስደተኞች ላይ ደርሰዋል ከተባሉት በደሎች መካከል ናቸው። የዓለም ስደተኞች ቀን በሚከበርበት ዕለት ኢትዮጵያ የስደተኞችን ደህንነት ለማስጠበቅ ምን እየሰራች ነው ስንል ጠይቀናል? ለዚህ እና ለሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች መልስ የሰጡን ደግሞ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት የኮሚኒኬሽን እና ውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ በአካል ንጉሴ ናቸው። ያነጋገራቸው ሀብታሙ ስዩም ነው።(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።)
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 05, 2023
በድባቴ እና እራስን በማጥፋት ስሜት ውስጥ ያሉ ወጣቶች ስለአዕምሮ ጤና የሚወያዩበት ቡድን
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
ጠያቂ ፊልሞች - ቆይታ ከፊልም ባለሞያ አቤል መካሻ ጋር
-
ፌብሩወሪ 04, 2023
በሜሪላንድ ግዛት የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ሊጀመር ነው
-
ፌብሩወሪ 03, 2023
ጋቢና ቪኦኤ
-
ፌብሩወሪ 02, 2023
ጋቢና ቪኦኤ
-
ፌብሩወሪ 01, 2023
ጋቢና ቪኦኤ