ኢትዮጵያ የስደተኞችን ደህንነት ለማስጠበቅ ምን እየሰራች ነው?
በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽን ሪፖርት መሰረት ኢትዮጵያ ከ800 ሺ በላይ ስደተኞችን በግዛቷ በማስጠለል ፣ በብዛት ስደተኞችን ከአስተናገዱ የአፍሪካ ሀገራት ሶስተኛ ደረጃ ላይ የምትገኝ ሀገር ናት። ሀገሪቱ በቅርብ ጊዜያት በርስበርስ ጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል። ።የጦርነቱ ጉዳት በዜጎቿ ላይ ብቻ ሳይሆን የተሻለ ህይወት ፈልገው በግዛቷ ለተጠለሉት ስደተኞችም መትረፉን የተለያዩ ሪፖርቶች ያሳያሉ ። የመጠለያ ጣቢያዎች ውድመት፣ የጭካኔ ተግባራት እና ሞት በስደተኞች ላይ ደርሰዋል ከተባሉት በደሎች መካከል ናቸው። የዓለም ስደተኞች ቀን በሚከበርበት ዕለት ኢትዮጵያ የስደተኞችን ደህንነት ለማስጠበቅ ምን እየሰራች ነው ስንል ጠይቀናል? ለዚህ እና ለሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች መልስ የሰጡን ደግሞ የስደተኞች እና ተመላሾች አገልግሎት የኮሚኒኬሽን እና ውጭ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ በአካል ንጉሴ ናቸው። ያነጋገራቸው ሀብታሙ ስዩም ነው።(ዝርዝሩን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡት።)
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጃንዩወሪ 18, 2025
በሩዋንዳ የማርበርግ ወረርሽኝ እና የሕክምና ባለሞያዋ ተሞክሮ
-
ጃንዩወሪ 18, 2025
የዱር እንስሳት መብት ተሟጋቿ ግሬታ ዩሪ
-
ጃንዩወሪ 17, 2025
ጋቢና ቪኦኤ
-
ጃንዩወሪ 12, 2025
የጎዳና ላይ ተዳዳሪዎችን ገላ የሚያጥቡት በጎ ፈቃደኞች
-
ጃንዩወሪ 11, 2025
"ልጄስ" ተከታታይ ድራማ በፓን አፍሪካን ፊልም ፌስቲቫል ላይ በሁለት ዘርፎች ተሸለመ
-
ጃንዩወሪ 10, 2025
ጋቢና ቪኦኤ