በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ራያ ቆቦ ወረዳ የሚገኙ ስምንት ቦታዎች በህወሓት ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለፁ


ራያ ቆቦ ወረዳ የሚገኙ ስምንት ቦታዎች በህወሓት ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ነዋሪዎች ገለፁ
please wait

No media source currently available

0:00 0:05:56 0:00

የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን ተከትሎ ተከትሎ ከራያ ቆቦ የተለያዩ ወረዳዎች እንዲሁም ከአላማጣና ከአጎራባች አካባቢዎች የተፈናቀሉ ሰባ ሺሕ የሚገመቱ ተፈናቃዮች በቆቦ፣ ሮቢት፣ ጎብዬና ወልዲያ ከተሞች እንዲሁም በድሌሮቃ ጃራ መጠለያ ጣቢያዎች ተጠልለው እንደሚገኙ ተፈናቃዮቹ ይናገራሉ።

በአሁኑ ሰዓትም የህወሓት ታጣቂዎች በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ራያ ቆቦ ወረዳ የሚገኙ ስምንት አካባቢዎችን ሙሉ በሙሉ እና በከፊል መቆጣጠራቸውን ነዋሪዎች እና ፖሊስ ገልጿል።

ከህወሓት በኩል ለሰላም ማንኛውንም ጥረት እንደሚያደርጉ፣ በአንጻሩ ትግራይ ክልል ከበባ ውስጥ መሆኑን ከመግለጽ ባለፈ ተይዘዋል ስለተባሉት ቀበሌዎችም ሆነ በአዲስ ቅኝና አካባቢዎቹ ተፈጸመ ስለተባለው ዘረፋ የተሰጠ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ የለም፡፡

XS
SM
MD
LG