የጥንታዊ ኢትዮጵያን ታሪክ ያጠኑት ሊቅ ፕሮፌሰር ጌታቸው ሀይሌ ልጅ፣ ርብቃ ሀይሌ በስደት ለ25 አመታት በኖረችበት አሜሪካን ሀገር የስደት ህይወትን ለማሸነፍ እና በህግ ትምህርት ትልቅ ቦታ ለመድረስ የረዳትን ጥራት ያለው ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ ለመውሰድ የኢትዮጵያ ትምህርት ተነሳሽነት ተቋም በመመስረት ዓለም አቀፍ ድረጃው የጠበቀ ትምህርት መስጠት ጀምራለች። ተቋሙ በደብረብርሃን የከፈተው ሀይሌ ማናስ አካዳሚ አዳሪ ትምህርትቤት 400 የሁለተኛ ድረጃ ተማሪዎችን ከመላው ኢትዮጵያ ተቀብሎ ማስተማር የሚችል አቅም ያለው ሲሆን የአመራርና ማህበረሰብን የመገንባት ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን የማፍራት እቅድ አለው። ስመኝሽ የቆየ ርብቃ በተለይ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እያደረገች ስላለችው ጥረት አነጋግራታለች።
የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል አልማ የተነሳችው ኢትዮጵያዊት - ርብቃ ሀይሌ
የፕሮፌሰር ጌታቸው ሀይሌ ልጅ፣ ርብቃ ሀይሌ የስደት ህይወትን ለማሸነፍ የረዳትን ጥራት ያለው ትምህርት ወደ ኢትዮጵያ ለመውሰድ የኢትዮጵያ ትምህርት ተነሳሽነት ተቋም በመመስረት ዓለም አቀፍ ድረጃውን የጠበቀ ትምህርት መስጠት ጀምራለች። ተቋሙ በደብረብርሃን የከፈተው ሀይሌ ማናስ አካዳሚ አዳሪ ትምህርትቤት 400 የሁለተኛ ድረጃ ተማሪዎችን ከመላው ኢትዮጵያ ተቀብሎ ማስተማር የሚችል ሲሆን የአመራርና ማህበረሰብን የመገንባት ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን የማፍራት እቅድ አለው።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
የኢሮብ ብሔረሰብ የመበታተን አደጋ እንደተጋረጠበት ተገለጸ
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
በጎንደር ከባድ በተባለ ዐዲስ ውጊያ የከተማዋ እንቅስቃሴ እንደተስተጓጎለ ነው
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
የኢዜማ ፓርቲ ሊቀ መንበር ዶር. ጫኔ ከበደ በፖሊስ እንደተያዙ ተነገረ
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
በአፋር ክልል መጋሌ ወረዳ የምግብ እጥረት ለሞት የሚዳርግ የጤና ችግር እንዳስከተለ ተገለጸ
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
የማራቶን ሬከርድ ወደ ኢትዮጵያ በመመለሱ እንደተደሰተች አትሌው ትዕግሥት አሰፋ ገለጸች
-
ሴፕቴምበር 25, 2023
የዐዲስ አበባው የሕዳሴ ግድብ ድርድር ያለስምምነት ተጠናቋል