በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ቻይናውያን አሰሪዎች የሚፈጽሙት የመብት ጥሰት አፍሪካ ያላትን ገጽታ እያጎደፈው ነው?


ቻይናውያን አሰሪዎች የሚፈጽሙት የመብት ጥሰት አፍሪካ ያላትን ገጽታ እያጎደፈው ነው?
please wait

No media source currently available

0:00 0:03:58 0:00

ሩዋንዳ ውስጥ አንድ የቻይና ኩባኒያ አሠሪ ከግንድ ጋር የታሰረ ሠራተኛን ሲገርፍ የሚያሳየው የቪዲዮ ምስል ከአፍሪካውያን አዕምሮ አልጠፋም። በአህጉሪቱ ዙሪያ ቁጣ ቀስቅሷል። የሩዋንዳ ፍርድ ቤት ድርጊቱን በሠራተኛው ላይ የፈጸመውን ሱን ሹጁን የተባለውን ቻይናዊ የማዕድን ቁፋሮ ሥራ አስኪያጅ የሃያ ዓመት እስራት ቅጣት ወስኖበታል። በአፍሪካ ሀገሮች ቻይናውያን አሠሪዎች ሠራተኞቻቸው ላይ የሚያደርሱት የማሰቃየት ድርጊት በስፋት የሚታይ መሆኑን ጉዳዩን የሚከታተሉ አዋቂዎች ይናገራሉ፡፡

ከደቡብ አፍሪካ ጆሀንስበርግ ከተማ ኬት ባርትሌት ያጠናቀረችውን ሪፖርት ቆንጅት ታየ ወደ አማርኛ መልሳዋለች፡፡

XS
SM
MD
LG