በዌስተርን ዩኒየን ፋውንዴሽን ድጋፍ በየአመቱ በካናዳ የሚዘጋጀው የምርጥ ስደተኞች ሽልማት ዘንድሮ በሰኔ ወር ላይ ለ14ኛ ግዜ ይካሄዳል። ሽልማቱ በስደት ወደ ካናዳ ሄደው ለስኬት የበቁ እና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ድምፅ መሆን ለቻሉ ሰዎች የተዘጋጀ ሲሆን ዘንድሮ እጩ ሆነው ከቀረቡ 25 ሰዎች መሃከል አንዷ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ መሰረት ሀይለየሱስ ናት። ለ10 አመታት በካናዳ የኖረችው መሰረት ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ፍትህ እንዲያገኙና ራሳቸውን እንዲችሉ የሚንቀሳቀስ Canadian Centre for Women's Empowerment የተሰኘ ተቋም ስራ አስኪያጅ ስትሆን በጤና አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያም ትሰራለች። እ.አ.አ በ2016 ካናዳ የተሻለ ሀገር እንድትሆን ካደረጉ 150 ሴቶች መሃል አንዷ ሆና ተመርጣ የነበር ሲሆን ባለፈው አመት በካናዳ ከአርባ አመት እድሜ በታች ሆነው ስኬታማ መሆን ከቻሉ 40 ሰዎች መሃል አንዷ መሆንም ችላለች። በተጨማሪም ባለፈው አመት ከካናዳ የፓርላማ አባልና የኢኮኖሚ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ንግድ ሚኒስቴር እጅ ብሄራዊ ሽልማት አግኝታለች። ስመኝሽ የቆየ መሰረት በምትሰራቸው ማህበራዊ እና ፍትሃዊ ንቅናቄዎች ዙሪያ አናግራታለች፣ቀጥሎ ይቀርባል።
"እርግዝና የሞት ፍርድ መሆን የለበትም" መሰረት ሀይለየሱስ፣ የምርጥ ስደተኛ ሽልማት እጩ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 19, 2025
የኦክላሆማ ግዛት ትምህርት ቤቶች የተማሪዎችን የኢሚግሬሽን ኹኔታ ለመመዝገብ ዐቅደዋል
-
ፌብሩወሪ 19, 2025
የአውሮፓ መሪዎች በዩክሬንና በአህጉሩ ጸጥታዊ ጉዳዮች ላይ አስቸኳይ ጉባኤ አካሔዱ
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
ስደተኞችን የማባረሩ ሂደት በካሊፎርኒያ የእርሻ ሠራተኞች ላይ ስጋት ፈጥሯል
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
ትግራይ ክልል ለፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ ተፈጻሚነት ጥሪ አቀረበ
-
ፌብሩወሪ 17, 2025
በኬንያ ከግንቦት ወር ወዲህ 82 ሰዎች በግዳጅ ተሰውረዋል - የኬንያ ሰብአዊ መብት ቡድን