በዌስተርን ዩኒየን ፋውንዴሽን ድጋፍ በየአመቱ በካናዳ የሚዘጋጀው የምርጥ ስደተኞች ሽልማት ዘንድሮ በሰኔ ወር ላይ ለ14ኛ ግዜ ይካሄዳል። ሽልማቱ በስደት ወደ ካናዳ ሄደው ለስኬት የበቁ እና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ድምፅ መሆን ለቻሉ ሰዎች የተዘጋጀ ሲሆን ዘንድሮ እጩ ሆነው ከቀረቡ 25 ሰዎች መሃከል አንዷ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ መሰረት ሀይለየሱስ ናት። ለ10 አመታት በካናዳ የኖረችው መሰረት ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ፍትህ እንዲያገኙና ራሳቸውን እንዲችሉ የሚንቀሳቀስ Canadian Centre for Women's Empowerment የተሰኘ ተቋም ስራ አስኪያጅ ስትሆን በጤና አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያም ትሰራለች። እ.አ.አ በ2016 ካናዳ የተሻለ ሀገር እንድትሆን ካደረጉ 150 ሴቶች መሃል አንዷ ሆና ተመርጣ የነበር ሲሆን ባለፈው አመት በካናዳ ከአርባ አመት እድሜ በታች ሆነው ስኬታማ መሆን ከቻሉ 40 ሰዎች መሃል አንዷ መሆንም ችላለች። በተጨማሪም ባለፈው አመት ከካናዳ የፓርላማ አባልና የኢኮኖሚ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ንግድ ሚኒስቴር እጅ ብሄራዊ ሽልማት አግኝታለች። ስመኝሽ የቆየ መሰረት በምትሰራቸው ማህበራዊ እና ፍትሃዊ ንቅናቄዎች ዙሪያ አናግራታለች፣ቀጥሎ ይቀርባል።
"እርግዝና የሞት ፍርድ መሆን የለበትም" መሰረት ሀይለየሱስ፣ የምርጥ ስደተኛ ሽልማት እጩ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ዲሴምበር 04, 2023
በቫሌንሺያው ማራቶን ኢትዮጵያውያን በሁለቱም ጾታዎች አሸነፉ
-
ዲሴምበር 04, 2023
በየሳምንቱ ሰኞ የሚቀርበው አፍሪካ ነክ ርእሶች
-
ዲሴምበር 04, 2023
በዐማራ ክልል የኮሌራ ወረርሽኝ የ90 ሰዎች ሕይወት እንዳለፈ ተገለጸ
-
ዲሴምበር 04, 2023
በእስራኤል-ሐማስ ጦርነት ዐዲስ የተኩስ አቁም ስምምነት የማይጨበጥ ኾኗል
-
ዲሴምበር 04, 2023
ኢትዮጵያ የሠራተኞች የደመወዝ ወለል ስምምነትን እንድታጸድቅ የሥራ ድርጅቱ ጠየቀ
-
ዲሴምበር 04, 2023
በሰሜን ጎንደር ዞን ሦስት ወረዳዎች አራት ሰዎች በረኀብ እንደሞቱ ተገለጸ