በዌስተርን ዩኒየን ፋውንዴሽን ድጋፍ በየአመቱ በካናዳ የሚዘጋጀው የምርጥ ስደተኞች ሽልማት ዘንድሮ በሰኔ ወር ላይ ለ14ኛ ግዜ ይካሄዳል። ሽልማቱ በስደት ወደ ካናዳ ሄደው ለስኬት የበቁ እና ከራሳቸው አልፈው ለሌሎች ድምፅ መሆን ለቻሉ ሰዎች የተዘጋጀ ሲሆን ዘንድሮ እጩ ሆነው ከቀረቡ 25 ሰዎች መሃከል አንዷ ትውልደ ኢትዮጵያዊቷ መሰረት ሀይለየሱስ ናት። ለ10 አመታት በካናዳ የኖረችው መሰረት ሴቶች ኢኮኖሚያዊ ፍትህ እንዲያገኙና ራሳቸውን እንዲችሉ የሚንቀሳቀስ Canadian Centre for Women's Empowerment የተሰኘ ተቋም ስራ አስኪያጅ ስትሆን በጤና አገልግሎት ተደራሽነት ዙሪያም ትሰራለች። እ.አ.አ በ2016 ካናዳ የተሻለ ሀገር እንድትሆን ካደረጉ 150 ሴቶች መሃል አንዷ ሆና ተመርጣ የነበር ሲሆን ባለፈው አመት በካናዳ ከአርባ አመት እድሜ በታች ሆነው ስኬታማ መሆን ከቻሉ 40 ሰዎች መሃል አንዷ መሆንም ችላለች። በተጨማሪም ባለፈው አመት ከካናዳ የፓርላማ አባልና የኢኮኖሚ ልማት፣ ስራ ፈጠራ እና ንግድ ሚኒስቴር እጅ ብሄራዊ ሽልማት አግኝታለች። ስመኝሽ የቆየ መሰረት በምትሰራቸው ማህበራዊ እና ፍትሃዊ ንቅናቄዎች ዙሪያ አናግራታለች፣ቀጥሎ ይቀርባል።
"እርግዝና የሞት ፍርድ መሆን የለበትም" መሰረት ሀይለየሱስ፣ የምርጥ ስደተኛ ሽልማት እጩ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ኦክቶበር 21, 2024
የኤሌክቶራል ኮሌጅ ሂደት
-
ኦክቶበር 21, 2024
አፍሪካ በፀጥታው ምክር ቤት በሁለት ቋሚ አባል ሀገራት መወከል እንደሚገባት ጉተሬዥ ተናገሩ
-
ኦክቶበር 18, 2024
ድንበር አቋርጠው የሚገቡ ሕገ ወጥ ስደተኞች እና የደኅንነት ጉዳይ
-
ኦክቶበር 18, 2024
ቱርክ በአፍሪካ ቀንድ ያሏትን ግቦች አደጋ ላይ የጣለው የሶማሊያና የኢትዮጵያ ግንኙነት
-
ኦክቶበር 17, 2024
ከጥቅምቱ የአሜሪካ ምርጫ ጋር ተያይዞ የሚመጣ የአይምሮ ጭንቀት
-
ኦክቶበር 16, 2024
የኢትዮ ቴሌኮም 10 በመቶ ድርሻ ሽያጭ ዛሬ መጀመሩን ጠ/ሚኒስትር ዐቢይ አስታወቁ