በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ሞስኮ 13 የእንግሊዝ ከፍተኛ ባለስልጣናት ወደ ራሻ እንዳይገቡ አገደች


ከግራ ወደ ቀኝ የብሪታንያ የመከላከያ ሚኒስትር ቤን ዋላስ ፣ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትሩስ እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር የካቲት 24/2022 ዓ.ም ለንደን ፓርላማ ውስጥ ስብሰባ ላይ ተቀምጠው ያሳያል/ ፎቶ ፋይል
ከግራ ወደ ቀኝ የብሪታንያ የመከላከያ ሚኒስትር ቤን ዋላስ ፣ የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጠቅላይ ሚኒስትር ቦሪስ ጆንሰን እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሊዝ ትሩስ እንደ አውሮፓውያን የቀን አቆጣጠር የካቲት 24/2022 ዓ.ም ለንደን ፓርላማ ውስጥ ስብሰባ ላይ ተቀምጠው ያሳያል/ ፎቶ ፋይል

ሩሲያ - የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስቴር ቦሪስ ጆንሰን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ሊዝ ትረስ እና መከላከያ ሚኒስትሩን ቤንዋላስን እንዲሁም ሌሎች አስር የእንግሊዝ መንግስት አባላትና ፖለቲከኞች ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ ማገዷን የራሽያ የውጭጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ አስታውቋል።

ሩሲያ ውሳኔውን ያስተላለፈቸው የእንግሊዝ መንግስት ከዚህ ቀደም ታይቶ በማያውቅ ሁኔታ ባሳየችው ጠብ ጫሪነት እናበከፍተኛ የሩሲያ ባለስልጣናት ላይ በጣለችው ማዕቀብ ምክንያት መሆኑን፣ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ መግለጫአመልክቷል።

ክሬምሊን ለዩክሬን ጠንካራ ድጋፍ ያሳዩት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆንሰንን "ጸረ ሩሲያ ለመሆን በሚደረገው ሩጫ ዋናተሳታፊ" ስትል ገልፃቸዋለች።

ጆንሰን ከሳምንት በፊት ኪየቭ በመገኘት ከዩክሬን ፕሬዝዳንት ቩለድሚር ዚለንስኪ ጋር ተገናኝተው የነበረ ሲሆን ጦርነቱ ከተጀመረ አንስቶ ሁለቱ ሀገራት ላላቸው ትብብር ተመሰጋግነዋል።

XS
SM
MD
LG