በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

ጉተሬዥ የየመን ሁቲዎችን የነዳጅ ተቋማት ጥቃትና በሳኡዲ የሚመራውን የአየር ድብደባ አወገዙ


ትናንት ቅዳሜ እኤአ መጋቢት 26 2022 በየመን ዋና ከተማ በሳኡዲ አረብያ በሚመራው ጦር የአየር ጥቃት የደረሰውን ውድመት የመናውያን ሲመለከቱ
ትናንት ቅዳሜ እኤአ መጋቢት 26 2022 በየመን ዋና ከተማ በሳኡዲ አረብያ በሚመራው ጦር የአየር ጥቃት የደረሰውን ውድመት የመናውያን ሲመለከቱ

የተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጎተሬዥ ትናንት ቅዳሜ በሰጡት መግለጫ በየመን ሁቲ አማጽያንና የሳኡዲ መር ጦር መካከል የሚደረገውን የጥቃት ልውውጥ በማውገዝ እንዲቆም አሳስበዋል፡፡

አማጽያኑ በጅዳ አቅራቢያ በሳኡዲ የነዳጅ ማምረቻ ተቋማት ላይ ባላፈው ዓርብ ጥቃት አድርሰዋል፡፡

በሳኡዲ አረብያ የሚመራው የጥምረት ጦርም በየመን ዋና ከተማ ሰነዓ እና የሰአብዊ እርዳታ አቅርቦት መግቢያ በሆነችው በሆዲዳ የወደብ ከተማ ባለፈው ቅዳሜ የአውሮፕላን ድብደባ አካሂዷል፡፡

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዳስታወቀው በድብደባው 8 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል፡፡

እኤአ 2014 በኢራን የሚመራውን የሁቲ ጦር ሰነዓን መቆጣጠሩን ተከትሎ በሳኡዲ አረብያ የሚመራው ጦር ጣልቃ በመግባት የየመንን መንግስት መደገፍ ከጀመረ ሰባተኛው ዓመቱን መያዙ ተነገሯል፡፡

XS
SM
MD
LG