አጭር ቆይታ ፦ከቀድሞዋ የወጣት አፍሪካዊያን የአመራር መርሀ-ግብር(YALI) ተሳታፊ ራህዋ ገ/መስቀል ጋር
በያመቱ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከመላ አፍሪካ የተመረጡ ወጣቶች በዩናይትድ ስቴትስ በሚገኙ የትምህርት ተቋማት በተለያዩ ዘርፎች የአጭር ጊዜ ትምህርት እና ስልጠና ይወስዳሉ ።ወደ ሀገራቸው ተመልሰው የተማሩትን እንዲተገብሩም ይበረታታሉ። የማንዴላ ዋሺንግተን ፌሎሺፕ በተባለው በዚህ መርሀ ግብር ተሳታፊ የሆኑ ኢትዮጵያዊያን ፣ ወደ ሀገር ቤት ከተመለሱ በኃላ በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ መጠየቅ ከጀመርን ቆየት ብለናል ። ለዛሬ ወደ አንደኛው ተሳታፊ ራህዋ ገ/መስቀል ስልክ መተናል ።