የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ሃገራቸው የምትገኝበትን ሁኔታ የሚተነትን ንግግር ዛሬ ያደርጋሉ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ሃገራቸው የምትገኝበትን አጠቃላይ ሁኔታ የሚያብራራ የመጀመሪያ ዓመታዊ ንግግራቸውን ለተወካዮች ምክር ቤቱ ጥምር ጉባዔ ዋሺንግተን ዲሲ ላይ ዛሬ ከምሽቱ ሦስት ሠዓት፤ በዓለምአቀፍ ሠዓት አቆጣጠር 0200 ጂኤቲ ወይም ለንደን ላይ ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት፤ በአዲስ አበባ ጊዜ ከንጋቱ 11፡00 ሠዓት ላይ ያደርጋሉ። ፕሬዚዳንት ባይደን ያነሷቸዋል ተብለው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል የሩሲያ የዩክሬን ወረራ፣ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን፣ እንዲሁም የሃገራቸው ምጣኔ ኃብት ይገኙባቸዋል። ፕሬዚዳንት ባይደን ንግግራቸውን እንደጨረሱ የአዮዋ አገረ ገዥ ኪም ሬይኖልድስ የሪፐብሊካን ፓርቲውን ምላሽ ያሰማሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 08, 2025
የፖለቲካ ምርጫ እና ጭንቀት
-
ፌብሩወሪ 06, 2025
ያለ ዕድሜ ጋብቻና የሴት ልጅ ግርዛትን ለማስቆም ያስችላሉ የተባሉ ሰነዶች ይፋ ሆኑ
-
ፌብሩወሪ 06, 2025
የሃይማኖት ተቋማት መሪዎች የፀሎት እና የሰላም ጥሪ አቀረቡ
-
ፌብሩወሪ 05, 2025
በካልፎርኒያው ቃጠሎ ጉዳይ የኤዲሰን የኤሌክትሪክ አከፋፋይ ኩባንያ ተከሰሰ
-
ፌብሩወሪ 05, 2025
"ዩናይትድ ስቴትስ በጦርነት የዳሸቀቸውን ጋዛን ትይዛለች" ፕሬዝደንት ትረምፕ