በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የወባ ወረርሽኝ ሥርጭት መጨመር በደቡብ ክልል


የወባ ወረርሽኝ ሥርጭት መጨመር በደቡብ ክልል
please wait

No media source currently available

0:00 0:08:04 0:00

የወባ ወረርሽኝ ሥርጭት መጨመር በደቡብ ክልል

ከዐስር ዓመታት በኋላ እንደገና በተቀሰቀሰው የወባ ወረርሽኝ ባለፉት ስድስት ወራት 24 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን የደቡብ ክልል ጤና ቢሮ አስታወቀ።

የወረርሽኙ የሥርጭት መጠንም 23 በመቶ መጨመሩን የክልሉ ጤና ቢሮ የበሽታ መከላከል እና ጤና ማጎልበት ዳይሬክቶሬት ዲሬክቴር አቶ ማሌ ማቴ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።

በሽታው እንደ አዲስ መሰራጨት የጀመረው የኬሚካል ርጭት ባለመካሄዱ፣ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይለገስ የነበረው የአልጋ አጎበር በመቋረጡና በመዘናጋር ምክኒያት ተገልጿል። ስርጭቱን ለመግታትም የተጓደሉ ነገሮችን ማሟላት እንደሚያስፈልግ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።

XS
SM
MD
LG