በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

የሰላም ፖሊሲው ረቂቅ ተዋወቀ


የሰላም ፖሊሲው ረቂቅ ተዋወቀ
please wait

No media source currently available

0:00 0:06:52 0:00

የኢትዮጵያ የሰላም ሚኒስቴር ያወጣው “የሰላም ግንባታ ፖሊሲ” ረቂቅ በአገር በቀል ዕውቀቶችና በማኅበረሰባዊ አስተሳሳቦች ላይ የተመሠረተ መሆኑን የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ለቪኦኤ ተናግረዋል።

ፖሊሲው ሃገሪቱ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ያጣችውን ሰላም መልሳ እንድታረጋግጥ ሊያግዛት እንደሚችል ምሁራኑ ጠቁመው “ጠንካራና ደካማ ጎኖቹ” ያሏቸውን ሃሳቦችም አንስተው ተችተዋል።

በተለያየ ጊዜ ውይይት እንደተደረገበት የተገለጠው የፖሊሲው ረቂቅ ከሁለት ሣምንት በፊት ሃዋሳ በተካሄደ ጉባዔ እንዲተዋወቅ ተደርጓል። ፖሊሲስውን ያስተዋውቁት የሰላም ሚኒስትር ደ’ኤታው አቶ ታየ ደንዳአ ፖሊሲው የሚነሳው ከግጭቶች ትንተና ሳይሆን ኢትዮጵያዊያንን በትውልዶች ቅብብሎሽ ዘመናትን አሻግረዋል ካሉት የሰላምና የአብሮነት አስተሳሰብ መሆኑን አመልክተዋል።

XS
SM
MD
LG