አዲሱ የኮሮና ቫይረስ ልውጥ ዝርያ አሚክሮን በዓለም ላይ ታይቶ በማይታወቅ ፍጥነት እየተሰራጨ ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስጠንቅቋል። በተለይ የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት ስርጭት በአፍሪካ ዝቅተኛ መሆን ችግሩን የበለጠ እንደሚያባብሰው የጤና ባለሙያዎች ያስጠነቅቃሉ። ይህን አስመልክቶ ያነጋገርናቸው በደቡብ አፍርካ የህክማና ባለሙያዎች ፕሬዝዳንት የሆኑትና አዲሱን የኮቪድ ቫይረስ ዝርያ ያገኙት ዶክተር አንጀሊክ ኮቴዝ፣ አፍሪካ ክትባቱን በእኩል ደረጃ አግኝታ ቫይረሱን መቆጣጠር ካልቻለች፣ ቀሪው ዓለም ብቻውን ከስጋት ነፃ መሆን አይችልም ይላሉ።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ሜይ 19, 2022
ጄኔራል ተፈራ ማሞ ባህርዳር እንደሚገኙ ጠበቃቸው ገለፁ
-
ሜይ 19, 2022
የትግራይ ክልል መንግሥት የጦር ምርኮኞች እንዲለቀቁ መወሰኑን አስታወቀ