በቀላሉ የመሥሪያ ማገናኛዎች

በካመሩን የእግር ኳስ ሜዳ በተፈጠረ መረጋገጥ የሞትና መቁሰል አደጋ ደረሰ


በካመሩን የእግር ኳስ ሜዳ በተፈጠረ መረጋገጥ የሞትና መቁሰል አደጋ ደረሰ
please wait

No media source currently available

0:00 0:01:54 0:00

በካመሩን የአፍሪካ ዋንጫ ግጥሚያ እየተካሄደበት በነበረበት የእግር ኳስ ሜዳ በተፈጠረ መረጋገጥ ቢያንስ ስምንት ሰዎች ሲሞቱ 38 ስዎች ለጉዳት ተዳርገዋል።

ችግሩ የተከሰተው በካሜሩን እና ኮሞሮስ መሃከል ሊካሄድ የነበረውን ግጥሚያ ለመመልከት ኦሌምቤ ወደ ተሰኘው የእግር ኳስ ሜዳ ይገቡ የነበሩ ደጋፊዎች ቁጥር ሥርዓት ከሚያስከብሩ በመቶዎች ከሚቆጠሩ ፖሊሶች በልጦ ከፍተኛ በመሆኑ በተፈጠረ ግርግር መሆኑ ተመልክቷል፡፡
ካሜሩን እና የአፍሪካ የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ምርመራ እንዲካሄድ አዘዋል።
ሞኪ ኤድዊን ኪንዛካ፣ ከያውንዴ ያደረሰን ዘገባ ነው።
XS
SM
MD
LG