No media source currently available
የኢትዮጵያ ገና በዓል በታሪካዊቷ ላሊበላ በርካታ ታዳሚያን በተገኙበት በኃይማኖታዊ ስነስርዓቶች ደምቆ ተከብሯል። በክብረበዓሉ ላይ የተገኙት ፕሬዚደንት ሳህለወርቅ ዘውዴ፣ ላሊበላን ወደቀድሞ የቱሪስት ማዕከልነቷ ለመመለስ ኅብረተሰቡ የሚጠበቅበትን እንዲወጣ የጠየቁ ሲሆን ሀገራዊ መልዕክትም አስተላልፈዋል። ከተለያዩ ስፍራዎች የተገኙ ታዳሚዎችንም አስተያየት ያካተተው ዘጋቢያችን ኬኔዲ አባተ ከላሊበላ ከተማ ያሰናዳውን ዘገባ ከተያያዘው ፍይል ይመልከቱ።