የልብ ቀዶ ጥገና በኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሙያዎች መሰጠት በጀመረ ባለፉት በአራት አመታት ውስጥ በየአመቱ እስከመቶ የሚደርሱ የልብ ታማሚዎች በሀገር ውስጥ ያለምንም ወጪ ይታከማሉ። እነዚህን ውስብስብና አስቸጋሪ የቀዶ ህክምና ከሚያከናውኑት ሐኪሞች መካከል አንዱና በኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ማዕከል የሚሰሩት ዶክተር ፈቀደ አግዋር እስካሁን በግላቸው 312 ስኬታማ የልብ ቀዶ ጥገና ያከናወኑ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ እጅግ ፈታኝ የነበሩትንና በስኬት የተጠናቀቁ የቀዶ ጥገናዎችን የሚተርክ 'የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ' የሚል መፅሀፍ አሳትመዋል። ስመኝሽ የቆየ በመፅሃፉና በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና አሁን ያለበት ደረጃ ዙሪያ ከዶክተር ፈቀደ ጋር ቆይታ አድርጋለች።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 12, 2025
ትረምፕ በብረታ ብረት እና አሉሚነም ላይ የ25 ከመቶ ቀረጥ ጣሉ
-
ፌብሩወሪ 12, 2025
በዳርፉር የተፈናቃዮች መጠለያ ሕፃናት በረሃብ እየሞቱ ነው
-
ፌብሩወሪ 12, 2025
አቶ ልደቱ በሌላ አየር መንገድ ወደ ሀገራቸው ለመመለስ መዘጋታቸውን ገለጹ
-
ፌብሩወሪ 12, 2025
በአማራ ክልል ቋራ ወረዳ ሦስት ሰዎች በኮሌራ ወረርሽኝ ሞቱ
-
ፌብሩወሪ 11, 2025
በሽረ እንዳስላሴ በአንድ መዝናኛ ስፍራ በተወረወረ የእጅ ቦምብ 17 ሰዎች ቆሰሉ
-
ፌብሩወሪ 11, 2025
ምስራቅ ወለጋ ውስጥ በመኪና አደጋ የ43 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ወረዳው አስታወቀ