የልብ ቀዶ ጥገና በኢትዮጵያውያን የህክምና ባለሙያዎች መሰጠት በጀመረ ባለፉት በአራት አመታት ውስጥ በየአመቱ እስከመቶ የሚደርሱ የልብ ታማሚዎች በሀገር ውስጥ ያለምንም ወጪ ይታከማሉ። እነዚህን ውስብስብና አስቸጋሪ የቀዶ ህክምና ከሚያከናውኑት ሐኪሞች መካከል አንዱና በኢትዮጵያ የልብ ሕክምና ማዕከል የሚሰሩት ዶክተር ፈቀደ አግዋር እስካሁን በግላቸው 312 ስኬታማ የልብ ቀዶ ጥገና ያከናወኑ ሲሆን ከነዚህ ውስጥ እጅግ ፈታኝ የነበሩትንና በስኬት የተጠናቀቁ የቀዶ ጥገናዎችን የሚተርክ 'የልብ ጠጋኙ ማስታወሻ' የሚል መፅሀፍ አሳትመዋል። ስመኝሽ የቆየ በመፅሃፉና በኢትዮጵያ የልብ ቀዶ ጥገና አሁን ያለበት ደረጃ ዙሪያ ከዶክተር ፈቀደ ጋር ቆይታ አድርጋለች።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ማርች 14, 2025
የባለ ሥልጣናት መፈታት ለደቡብ ሱዳን ውጥረት መርገብ ቁልፍ ጉዳይ ነው ተባለ
-
ማርች 14, 2025
የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥት በዶ.ር ደብረ ጽዮን የሚመራው የህወሓት ቡድን ወቀሰ
-
ማርች 14, 2025
አይኤምኤፍ እና ኢትዮጵያ በዋጋ ግሽበት ትንበያ ተለያዩ
-
ማርች 13, 2025
የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ሦስት አባላቱ መታሰራቸውን አስታወቀ
-
ማርች 12, 2025
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌደራል መንግሥቱን ጣልቃ ገብነት ጠየቀ
-
ማርች 12, 2025
በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ያገለገሉ 800 ሠራተኞች መታዳቸውን ገለጹ