No media source currently available
በደቡብ ክልል በ47 የምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደሚካሄድ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የደቡብ እና የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ አስታወቀ። ምርጫው ጳጉሜ 1/2013 የሚደረግ ሲሆን 22 የምርጫ ጣቢያዎች ሕዝብ ውሳኔ የሚካሄድባቸው ሲሆኑ የቀሩት ደግሞ ምርጫ ቦርድ እንደገና ምርጫው እንዲካሄድባቸው የወሰነባቸው እና በፀጥታ ችግር ምርጫ ያልተደረገባቸው መሆኑም ተገልጿል።