በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ስላቅ እና የምፀት ይዘት ያላቸውን የካርቱን ስራዎች በማውጣት የሚታወቀው የካርቱን ስዕል ባለሙያ አለማየሁ ተፈራ ለአመታት የሰራቸውን ስራዎች አሰባስቦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የካርቱን ስዕሎች ስብስብ የያዘ መፅሃፍ ከሰሞኑ ለገበያ አቅርቧል። ፈንጠዝያ የተሰኘው ይህ መፅሃፍ ከመቶ ሀምሳ በላይ በሆኑ ገፆቹ ወቅታዊና ነባራዊ የሆኑ የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚያነሱ የካርቱን ስራዎች የያዘ ሲሆን በተለይ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳዩ ስብስቦች እንዳሉት አለማየሁ ይናገራል። በዚህ ስራው ዙሪያ ከአለማየሁ ጋር ቆይታ ያደረገችው ስመኝሽ የቆየ ናት።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ኖቬምበር 29, 2023
ዩክሬን አጋሮቿ የመካላከያ ምርቶቻቸውን እንዲያሳድጉ ጠየቀች
-
ኖቬምበር 10, 2023
የዐድዋ ዜሮ ዜሮ ሙዝየም ሥነ ጥበብ ሥራዎች ዳግም እንዲታዩ ማኅበሩ ጠየቀ
-
ኦክቶበር 28, 2023
ህወሓት ለዛሬ በጠራው የካድሬ ስብሰባ ባጸደቀው አጀንዳ ላይ ነገ ይወያያል ተባለ
-
ኦክቶበር 11, 2023
ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲ ዐይን የቃኘ መጽሃፍ ለንባብ በቃ
-
ሴፕቴምበር 21, 2023
የአወዛጋቢዋ አውራ ጎዳና ወይም ቆርኬ ጥቃት አጠያያቂ እንደኾነ ነው