በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ ስላቅ እና የምፀት ይዘት ያላቸውን የካርቱን ስራዎች በማውጣት የሚታወቀው የካርቱን ስዕል ባለሙያ አለማየሁ ተፈራ ለአመታት የሰራቸውን ስራዎች አሰባስቦ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነውን የካርቱን ስዕሎች ስብስብ የያዘ መፅሃፍ ከሰሞኑ ለገበያ አቅርቧል። ፈንጠዝያ የተሰኘው ይህ መፅሃፍ ከመቶ ሀምሳ በላይ በሆኑ ገፆቹ ወቅታዊና ነባራዊ የሆኑ የፖለቲካና ማህበራዊ ጉዳዮችን የሚያነሱ የካርቱን ስራዎች የያዘ ሲሆን በተለይ ወቅታዊ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳዩ ስብስቦች እንዳሉት አለማየሁ ይናገራል። በዚህ ስራው ዙሪያ ከአለማየሁ ጋር ቆይታ ያደረገችው ስመኝሽ የቆየ ናት።
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጃንዩወሪ 21, 2023
የሚኒስትሮች ሹመት ለፓርላማ ቀረበ
-
ጃንዩወሪ 18, 2023
ራስን ማጥፋት የአይምሮ ጤና ቀውስ ውጤት ነው
-
ጃንዩወሪ 10, 2023
“ሸኔ” በተባሉ ታጣቂዎች በተከፈተ ጥቃት ሰዎች መገደላቸውና እስረኞች ማምለጣቸው ተነገረ
-
ጃንዩወሪ 10, 2023
የቀድሞ የብሔራዊ የመረጃ ደህንነት ም/ዋና ዳይሬክተር ዛሬ ከእስር ተለቀቁ
-
ጃንዩወሪ 07, 2023
ጉጂ ውስጥ ያለው የፀጥታ ችግር ለሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እንቅፋት ፈጥሯል - ኦቻ