No media source currently available
በኢትዮጵያ ለመጀምሪያ ጊዜ የድንገተኛ እና ጽኑ ህክምና አገልግሎት አሰጣጥ ጥራት እና ተደራሽነት ለመጨመር የሚያስችል የአምስት ዓመት መሪ ዕቅድ ባለፈው ሳምነት የጤና ሚኒስቴር ይፋ አድርጓል፡፡ መሪ እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግም 200 ሚሊየን ዶላር እንደሚያስፈልግ በኢትዮጵያ ጤና ሚኒስቴር የድንገተኛ እና ጽኑ ህክምና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑትን ዶ/ር አለኝታ ገብረየስ ለአሜሪካ ድምጽ ገልጸዋል፡