No media source currently available
በትግራይ ክልል ባለፉት አምስት ወራት የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝ ምርመራ አልተካሄደም ሲል የክልሉ ጤና ምርምር ተቋም አስታወቀ። ተቋሙ እንደገለፀው በክልል አሁን ባለው የፀጥታ ችግርና በጤና ተቋማት ላይ በደረሰው ጉዳት የኮቪድ-19 ምርመራ ለማካሄድ አዳጋች እንዳደረገው ገልጿል። በቅርብ ቀናት በመቀሌ ከተማ በሚገኙ የጤና ተቋማት የኮረና ምርመራ እየተጀመረ መሆኑን ተቋሙ አስታውቋል።