No media source currently available
የአውሮፓ ኅብረት በኤርትራ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ የኤርትራ መንግሥት አውግዟል። የአውሮፓ ኅብረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ትናንት መጋቢት 13/2013 ዓ.ም. በኤርትራ ላይ ያወጣውን የማዕቀብ ውሳኔ አስመልክቶ የሃገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ ኅብረቱ “ውሳኔውን በኤርትራ ላይ የማሳለፍ ህጋዊና ሞራላዊ ሥልጣን የለውም” ሲል ተቃውሞውን ገልጿል።