No media source currently available
በኢትዮጵያ በኅብረተሰቡ ዘንድ እየታየ ያለው መዘናጋት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስርጭትን ሊያባብሰው ስለሚችል ማኅበረሰቡ ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለበት የጤና ባለሞያዎች እየመከሩ ነው። የጉደር የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሕክምና ክፍል ኃላፊና የማዕከሉ ኮቪድ-19 ሕክምና አስተባባሪ ዶ/ር ናሆም ተሾመ፤ እርሳቸው በሚሠሩበት ሆስፒታል ውስጥ የታማሚዎች ቁጥር መጨመሩን ተናግረዋል።