No media source currently available
ዮዲት በቀለ ስታንቶን ነዋሪነቷን በእንግሊዝ ሃገር ያደረገች የቴክኖሎጂ የፈጠራ ባለሞያ ስትሆን ‘ኦፕን ሴንሰርስ’ የተሰኘ የቴክኖሎጂ ተቋም መስራች እና ዋና ስራ አስፈጻሚ ናት፡፡ ኦፕን ሴንሰርስ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ላሉ ትላልቅ ተቋማት የዓየር ብክለት መጠን መጠቆሚያ መሳሪያዎች ላይ ሶፍትዌር የሚገጥም ሲሆን፤ ዮዲት ለዚህ ፈጠራዋ መነሻ የሆናት የመጀመሪያ ልጇ የነበረባት የአስም ችግር እንደሆነም ትናገራለች፡፡