በግዙፉ የአሜሪካ የመድሃኒት አምራች ኩባንያ ፋይዘር እና የጀርመኑ የሕክምና ቴክኖሎጂ ኩባንያ ባዮ ኢንቴክ በጋራ የሰሩት የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት በአሜሪካን አገር መሰጠት ከጀመረ አንድ ሳምንት አስቆጠረ። በኒዮርክ ፍለ ግዛት Long Island Jewish በተሰኘ የጤና ተቋም ውስጥ የምትሰራዋ ነርስ ሳንድራ ሊንድሴይ የመጀመሪያውን ከቤተ ሙከራ ውጪ የተሰጠውን ክትባት ከወሰደች በኃላም በርካታ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው የሚሰሩ ባለሙያዎች በቅድሚያ ክትባቱን እየወሰዱ ይገኛሉ። ለመሆኑ የኮቪድ 19 ክትባት አወሳሰድ ምን አይነት ነው? ክትባቱ ከተወሰደ በኃላ የሚኖረው ስሜትስ ምን የምስላል? የሚሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ባለፈው ሳምንት ክትባቱን ከወሰዱ የመጀመሪያ የጤና ባለሙያዎች መሃል አንዱ የሆነውንና ኮሎራዶ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ቻፕሊን ሆኖ በሽተኞችን የማማከር አገልግሎት የሚሰጠውን ኢታና ጨመዳ ዲሳሳን ጋብዘናል።
ፋይዘር ያመረተውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት የወሰደ ኢትዮጵያዊ የህክምና ባለሙያ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጃንዩወሪ 25, 2021
በትግራይ ክልል የሕይወት አድን ድጋፍ እንዲፋጠን የአሜሪካ አምባሳደር አሳሰቡ
-
ጃንዩወሪ 25, 2021
የዓለም የጤና ድርጅት በትግራዩ ግጭት ወረርሽኝ ሊስፋፋ ይችላል አለ
-
ጃንዩወሪ 25, 2021
በትግራይ ክልል የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞች ጉዳይ
-
ጃንዩወሪ 25, 2021
አዴኃን በምርጫ ዙሪያ ለአባላቶቹ ሥልጠና ሰጠ
-
ጃንዩወሪ 25, 2021
በጋምቤላ ክልል እስር ቤቶች ላይ የኢሰመኮ ሪፖርት
-
ጃንዩወሪ 21, 2021
የፕሬዚዳንት ጆሴፍ አር ባይደን በዓለ ሲመት