በግዙፉ የአሜሪካ የመድሃኒት አምራች ኩባንያ ፋይዘር እና የጀርመኑ የሕክምና ቴክኖሎጂ ኩባንያ ባዮ ኢንቴክ በጋራ የሰሩት የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት በአሜሪካን አገር መሰጠት ከጀመረ አንድ ሳምንት አስቆጠረ። በኒዮርክ ፍለ ግዛት Long Island Jewish በተሰኘ የጤና ተቋም ውስጥ የምትሰራዋ ነርስ ሳንድራ ሊንድሴይ የመጀመሪያውን ከቤተ ሙከራ ውጪ የተሰጠውን ክትባት ከወሰደች በኃላም በርካታ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው የሚሰሩ ባለሙያዎች በቅድሚያ ክትባቱን እየወሰዱ ይገኛሉ። ለመሆኑ የኮቪድ 19 ክትባት አወሳሰድ ምን አይነት ነው? ክትባቱ ከተወሰደ በኃላ የሚኖረው ስሜትስ ምን የምስላል? የሚሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ባለፈው ሳምንት ክትባቱን ከወሰዱ የመጀመሪያ የጤና ባለሙያዎች መሃል አንዱ የሆነውንና ኮሎራዶ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ቻፕሊን ሆኖ በሽተኞችን የማማከር አገልግሎት የሚሰጠውን ኢታና ጨመዳ ዲሳሳን ጋብዘናል።
ፋይዘር ያመረተውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት የወሰደ ኢትዮጵያዊ የህክምና ባለሙያ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ጁላይ 27, 2024
1ሺሕ500 ስደተኞች ወደ አፍጥጥ መጠለያ መዛወራቸው ተገለጸ
-
ጁላይ 27, 2024
ከ17ሺሕ በላይ የራያ አላማጣ እና አካባቢው ተፈናቃዮች ተመለሱ
-
ጁላይ 26, 2024
ፓርላማው በመሬት መንሸራተት አደጋ ለሞቱ ወገኖች ብሔራዊ የኀዘን ቀን ዐዋጀ
-
ጁላይ 25, 2024
በህወሓት 14ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ዝግጅት የአመራሩ እና የቁጥጥር ኮሚሽኑ ውዝግብ