በግዙፉ የአሜሪካ የመድሃኒት አምራች ኩባንያ ፋይዘር እና የጀርመኑ የሕክምና ቴክኖሎጂ ኩባንያ ባዮ ኢንቴክ በጋራ የሰሩት የኮቪድ 19 መከላከያ ክትባት በአሜሪካን አገር መሰጠት ከጀመረ አንድ ሳምንት አስቆጠረ። በኒዮርክ ፍለ ግዛት Long Island Jewish በተሰኘ የጤና ተቋም ውስጥ የምትሰራዋ ነርስ ሳንድራ ሊንድሴይ የመጀመሪያውን ከቤተ ሙከራ ውጪ የተሰጠውን ክትባት ከወሰደች በኃላም በርካታ የጤና ባለሙያዎችና ሌሎች ለቫይረሱ ተጋላጭ ሆነው የሚሰሩ ባለሙያዎች በቅድሚያ ክትባቱን እየወሰዱ ይገኛሉ። ለመሆኑ የኮቪድ 19 ክትባት አወሳሰድ ምን አይነት ነው? ክትባቱ ከተወሰደ በኃላ የሚኖረው ስሜትስ ምን የምስላል? የሚሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ባለፈው ሳምንት ክትባቱን ከወሰዱ የመጀመሪያ የጤና ባለሙያዎች መሃል አንዱ የሆነውንና ኮሎራዶ ክፍለ ግዛት ውስጥ በሚገኝ ሆስፒታል ውስጥ ቻፕሊን ሆኖ በሽተኞችን የማማከር አገልግሎት የሚሰጠውን ኢታና ጨመዳ ዲሳሳን ጋብዘናል።
ፋይዘር ያመረተውን የኮሮና ቫይረስ ክትባት የወሰደ ኢትዮጵያዊ የህክምና ባለሙያ
የፕሮግራሙ ተከታታይ ክፍሎች
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
የፕሬዝዳንት ትራምፕ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ርምጃዎች እና ሉላዊ ተጽእኗቸው
-
ፌብሩወሪ 14, 2025
በሲዳማ ከአንድ ቤት ሦስት ህፃናት በቃጠሎ ሞቱ
-
ፌብሩወሪ 13, 2025
ህወሓት ከተፈናቃዮች "በግዳጅ የገንዘብ መዋጮ በመሰብሰብ" አቤቱታ ቀረበበት