No media source currently available
ኤልሻዳይ ግርማ በአትላንታ ጆርጂያ የቴክኖሎጂ ኢኒስቲትዩት የሶስተኛ ዓመት የአካባቢያዊ ምህንድስና ተማሪ እና የግሪን ኢትዮጵያ የድረገጽ እንቅስቃሴ መስራች ናት፡፡ የዘምቢል መልስ ኢትዮጵያን ከፕላስቲክ ከረጢቶች እና ምርቶች ነጻ በማውጣት አካባቢን የማጽዳት ዓላማ ይዞ የሚንቀሳቀሰ ሲሆን፤ ዘንቢልን የመሳሰሉ በድጋሚ ጥቅም ላይ የሚውሉ እንዲሁም አርጅተው ሲጣሉ አካባቢን የማይበክሉ መገበያያዎችን ሰዎች እንዲጠቀሙ እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡