ዋሽንግተን ዲሲ —
በሃያዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኘው ሀና ሀይሉ የወጣቶችን መንፈስ በሚያጠነክሩ ፣ ለበጎ ስራ በሚያነቃቁ ስልጠናዎች ብዙሃንን ለማገዝ እያጣረች ያለች ወጣት ናት።
ከተማሪነት ዘመኗ ጀምሮ ታደርጋቸው ከነበሩ ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች ያገኘቻቸውን ልምዶች ፣ ከህይወት ገጠመኞቿ ጋር አቀናጅታ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍል ለመጡ ወጣቶች በተለያዩ መድረኮች እያጋራች ትገኛለች።
ከስራዋ ጋር የተያያዙ ሀሳቦችን ተጋርተናል።