No media source currently available
ዕድሜዋ በሃያዎቹ መጀመሪያ ላይ የምትገኘው ሀና ሀይሉ የወጣቶችን መንፈስ በሚያበሩ ፣ ለበጎ ስራ በሚያነቃቁ ስልጠናዎች ብዙሃንን ለማገዝ እያጣረች ያለች ወጣት ናት።ከተማሪነት ዘመኗ ጀምሮ ታደርጋቸው ከነበሩ ማህበረሰብ አቀፍ ስራዎች ያገኘቻቸውን ልምዶች ፣ ከህይወት ገጠመኞቿ ጋር አቀናጅታ ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍል ለመጡ ወጣቶች በተለያዩ መድረኮች እያጋራች ትገኛለች። ከስራዋ ጋር ስለተያዩ ጉዳዮች አጭር ቆይታ አድርገናል።