No media source currently available
በዓለም ዙሪያ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ህይወት የቀጠፈው የኮሮና ቫይረስ በእናቶችና ህፃናት ጤና ላይ ተጨማሪ ስጋቶች ማስከተሉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታውቋል። በወረርሽኙ ምክንያት ለእናቶችና ህፃናት የሚሰጡ የጤና አገልግሎቶች ሀያ በመቶ በመቀነሳቸው፣ የእናቶች፣ አዲስ የሚወለዱ አና ታዳጊ ህፃናት ሞት ቁጥር መጨመሩም ተነግሯል። ዘገባው የካሮል ፒርሰን ነው፣ ስመኝሽ የቆየ ታቀርበዋለች።