No media source currently available
በኢትዮጵያ ህክምና ተቋማት በቂ ራስን ከኮሮና ቫይረስ መከላከያ ቁሳቁሶች ባለመኖሩና በአጠቃቀም ጉድለት የጤና ተቇማት ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ለቫይረሱ ተጋላጭነት በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ መሆኑን ቪኦኤ ያነጋገራቸው የህክምና ባለሙያዎች ገልፀዋል። የኢትዮጵያ የመድሃኒት አቅራቢ ኤጀንሲ በበኩሉ የህክምና ባለሙያዎችን ከወረርሽኙ ለመክላከል የሚያስፈልጉ የህክምና ግብአቶች እጥረት መኖሩን ገልፆ፣ በሚቀጥሉት አንድ ወራት ችግሩን ለመቅረፍ እየሰራን ነው ብሏል።